በኢትዮጵያ የመድኃኒት ብክነት መጠን ከ1 በመቶ በታች ደረሰ
20:01 31.08.2026 (የተሻሻለ: 20:04 31.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የመድኃኒት ብክነት መጠን ከ1 በመቶ በታች ደረሰ
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት የተቀናጀና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአቅርቦት ሰንሰለት አሠራር የመድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶች ብክነትን፤ ወደ 0.6% ዝቅ ማድረግ መቻሉን አስታውቋል።
ተቋሙ በዲጂታል ሥርዓት ትግበራ በሌሎች ሀገራት ረጅም ጊዜ የሚወስደውን ዓመታዊ የክምችት ቆጠራ በኢትዮጵያ መደበኛ ሥራ ሳይስተጓጎል ከ3 እስከ 4 ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅ መቻሉንም ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልጿል።
አገልግሎቱ በአሁኑ ወቅት ከ44% በላይ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት እየሸፈነ ሲሆን በሚቀጥሉት አራት ዓመታት 60% ለማድረስ እየሠራ ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X