የታክስ ስወራን ለመግታት በቢራ እና በለስላሳ መጠጦች ፋብሪካዎች ላይ የካሜራ ቁጥጥር ተጀመረ
18:47 31.08.2026 (የተሻሻለ: 18:54 31.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የታክስ ስወራን ለመግታት በቢራ እና በለስላሳ መጠጦች ፋብሪካዎች ላይ የካሜራ ቁጥጥር ተጀመረ
የገቢዎች ሚኒስቴር ኤክሳይዝ ታክስ የሚከፈልባቸውን እንደ ቢራ፣ የለስላሳ መጠጦች እና የትምባሆ ውጤቶች የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን የማምረትና የጭነት እንቅስቃሴ በቀጥታ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ካሜራዎች የመትከል ሥራ ጀምሯል።
የአዲሱ እርምጃዎች ቁልፍ ጉዳዮች፦
የመመሪያ ቁጥር 1079/2025 ድንጋጌ ምርቶች ላይ የሚለጠፉ አካላዊ ማህተሞች ወይም ዲጂታል ኮዶች እንዲኖሩ የሚያስገድድ ሲሆን ሚኒስቴሩ በዲጂታል መንገድ ከሩቅ ሆኖ ምርቶችን እንዲቆጣጠር ሥልጣን ይሰጣል።
መንግሥት ለዚህ የዲጂታል ቁጥጥር ሥራ 300 ሚሊዮን ብር የመደበ ሲሆን ፋብሪካዎች ቢያንስ ሁለት ካሜራዎችን በራሳቸው ወጪ እንዲተክሉ ተደርጓል።
የካሜራ ገጠማው በየፋብሪካው የማምረቻ መስመሮች፣ የማሸጊያ ቦታዎች እና የእቃ መጫኛ ክፍሎች ላይ ትክክለኛ ቁጥጥር በማድረግ ምርት የመሸሸግ እና የታክስ ስወራ ክፍተቶችን ለመዝጋት ያለመ ነው።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X