በኬንያ የአውሮፕላን ማረፊያ ሠራተኞች አድማ በሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞችን በረራ አስተጓጎለ - መገናኛ ብዙኃን

ሰብስክራይብ

በኬንያ የአውሮፕላን ማረፊያ ሠራተኞች አድማ በሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞችን በረራ አስተጓጎለ - መገናኛ ብዙኃን

በኬንያ ጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የተጀመረው የሥራ ማቆም አድማ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። የሠራተኞች ማኅበሩ ከኬንያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ጋር የጋራ ስምምነት መድረስ አለመቻሉን እና የትብብር እጦትን ጨምሮ የተለያዩ ቅሬታዎችን እያቀረበ እንደሚገኝ የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች አመልክተዋል።

የኬንያ አውሮፕላን ማረፊያዎች ባለሥልጣን በኤክስ ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ለተፈጠረው እንግልት ይቅርታ ጠይቆ፤ "መንገደኞች ስለ ወቅታዊ የበረራ ሁኔታ ከሚበሩበት አየር መንገድ መረጃ እንዲጠይቁ እና ጉዟቸውን በዚያው ልክ እንዲያቅዱ እንመክራለን" ብሏል።

ሩዋንድኤር በኬንያ አውሮፕላን ማረፊያ "የአየር ትራፊክ ቁጥጥር አገልግሎት ላይ ባጋጠሙ የአሠራር እክሎች ምክንያት" እሁድ እና ሰኞ ሊደረጉ የነበሩ በረራዎችን መሰረዙን በኤክስ ገጹ ገልጿል።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተወሰዱ ምሥሎች

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0