የሊቢያ ተፎካካሪ ወገኖች በሁለት ዓመታት ውስጥ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ - የተባበሩት መንግሥታት
08:04 31.08.2026 (የተሻሻለ: 09:45 31.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሊቢያ ተፎካካሪ ወገኖች በሁለት ዓመታት ውስጥ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ - የተባበሩት መንግሥታት
ከሊቢያ አራቱ ዋና ዋና ተቋማት የተወጣጡ ሁለት ሁለት ተወካዮች የተሳተፉበት እና "4+4" በመባል በሚታወቀው የውይይት መድረክ የተደረሰውን ይህን ስምምነት፣ እሁድ ዕለት በትሪፖሊ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሊቢያ ድጋፍ ተልዕኮ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመውታል።
የስምምነቱ ዋና ዋና ነጥቦች፡
🟠 ምርጫው በ24 ወራት ውስጥ በአንድ አስፈፃሚ አካል ስር እንዲካሄድ፤
🟠 በምርጫ ሕግ ማዕቀፍ ላይ ማሻሻያዎች እንዲጸድቁ፤
🟠 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የሀገር ከፍተኛ ምክር ቤት ስምምነቱን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያጸድቁት፤
🟠 እነዚህ አካላት ማጽደቅ ካልቻሉ፣ ወገኖቹ ስምምነቱን በሀገር በቀል አሰራሮች አማካኝነት እንደ ሕገ-መንግስታዊ ሰነድ ለማጽደቅ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደህንነት ምክር ቤት ድጋፍ ለማግኘት እንደሚሰሩ ተገልጿል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት የዋና ጸሐፊው ልዩ ተወካይ ሀና ቴቴ ፤ "የዛሬው ስምምነት በሊቢያ የምርጫ ሂደቱን አግዶ የቆየውን ፖለቲካዊ እና ተቋማዊ ውጥረት ለመፍታት ትልቅ እርምጃ ነው" ብለዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
ከሊቢያ አራቱ ዋና ዋና ተቋማት የተወጣጡ ሁለት ሁለት ተወካዮች የተሳተፉበት እና "4+4" በመባል በሚታወቀው የውይይት መድረክ የተደረሰውን ይህን ስምምነት፣ እሁድ ዕለት በትሪፖሊ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሊቢያ ድጋፍ ተልዕኮ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመውታል።
የስምምነቱ ዋና ዋና ነጥቦች፡
🟠 ምርጫው በ24 ወራት ውስጥ በአንድ አስፈፃሚ አካል ስር እንዲካሄድ፤
🟠 በምርጫ ሕግ ማዕቀፍ ላይ ማሻሻያዎች እንዲጸድቁ፤
🟠 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የሀገር ከፍተኛ ምክር ቤት ስምምነቱን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያጸድቁት፤
🟠 እነዚህ አካላት ማጽደቅ ካልቻሉ፣ ወገኖቹ ስምምነቱን በሀገር በቀል አሰራሮች አማካኝነት እንደ ሕገ-መንግስታዊ ሰነድ ለማጽደቅ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደህንነት ምክር ቤት ድጋፍ ለማግኘት እንደሚሰሩ ተገልጿል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት የዋና ጸሐፊው ልዩ ተወካይ ሀና ቴቴ ፤ "የዛሬው ስምምነት በሊቢያ የምርጫ ሂደቱን አግዶ የቆየውን ፖለቲካዊ እና ተቋማዊ ውጥረት ለመፍታት ትልቅ እርምጃ ነው" ብለዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X