የእሬት መድኃኒትነት እና የምርት መጠን ከሚበቅልበት ቦታ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት እንዳለው አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ
19:35 30.08.2026 (የተሻሻለ: 19:44 30.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የእሬት መድኃኒትነት እና የምርት መጠን ከሚበቅልበት ቦታ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት እንዳለው አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ
በኢትዮጵያውያን ተመራማሪዎች በሰሜን ሸዋ ዞን በተካሄደው ጥናት፣ የእሬት ተክል የሚበቅልበት ወረዳ እና ዝርያው ተክሉ የሚኖረውን የመድኃኒትነት ይዘት፣ የማዕድናት መጠን እና የቅጠል ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚወስነው ተረጋግጧል።
ዋና ዋና መረጃዎች
🟠 የተጠኑ አካባቢዎች (3 ወረዳዎች)፦ ከአንኮበር፣ ከመርሃቤቴ እና ከከዎት የተሰበሰቡ 6 የተለያዩ የእሬት ዝርያዎች በጋራ አንድ ቦታ ተተክለው ተመዝግበዋል።
🟠የከዎት እና የአንኮበር የእሬት ዝርያዎች ከፍተኛ የመድኃኒትነት ይዘት፣ የማዕድን ስብጥር እና ከፍተኛ የቅጠል ምርት በማስመዝገብ በግንባር ቀደምነት ተለይተዋል።
🟠 ጥናቱ አርሶ አደሮች ተክሉን "ወንዴ" እና "ሴቴ" እሬት ብለው የሚለዩበትን ባህላዊ እውቀት ሳይንሳዊ መሠረት ያለው መሆኑን አረጋግጧል።
🟠 ለመድኃኒት፣ ለሥነ-ውበት እና ለምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች እሬትን የዝርያ ጥራቱን ተመልክቶ መግዛት ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
"በተመሳሳይ እንክብካቤ የበቀሉ የእሬት ዓይነቶች እንኳን በመጡበት ቦታ እና በዘረመል ልዩነታቸው ምክንያት የሚሰጡት የጄል (የዝልግልግ ቅባት) መጠን እና የመድኃኒትነት ኃይል የተለያየ ነው፤ ይህም ለአርሶ አደሮች እና ለፋብሪካዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ይሰጣል" ሲል ዓለም አቀፉ 'ዲስከቨር ፕላንትስ' ጆርናል ላይ የታተመው ጥናት አመላክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X