የሱዳን ጉዳይ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች አወዛጋቢ አሠራሮችን አጋልጧል - ሱዳናዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ
የሱዳን ጉዳይ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች አወዛጋቢ አሠራሮችን አጋልጧል - ሱዳናዊ ባለሙያ

የተመድ የእውነታ አፈላላጊ ተልእኮን አስመልክቶ፣ በሱዳን እና በምዕራባውያን ኃይሎች መካከል የተፈጠረው ውጥረት በዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ሥርዓት ውስጥ ያለውን መሰረታዊ ግጭት ማለትም በተጠያቂነት እና በሉዓላዊነት መካከል ያለውን የሚዛን መዛባት እንደሚያሳይ ዶ/ር ሞሐመድ ሁሴን አብደልዋሂድ ሞሐመድለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ባለሙያው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

🟠 መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ላይ፦ ካርቱም የውጭ አካላት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማንቀሳቀስ በፈጥኖ ደራሹ ኃይሎች ትርክትን በሠራዊቱ ላይ ያሰፋፋሉ ስትል ላቀረበችው ክስ ባለሙያው በሰጡት ምላሽ፣ የሲቪል ማህበራት ጥሰቶችን በመሰነድ ረገድ ሕጋዊ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ አምነዋል። ሆኖም የገንዘብ ምንጫቸው እና ከዓለም አቀፍ አካላት ጋር ያላቸው ቁርኝት የግጭቱን ገጽታ አቀራረብ ለውጠው ስለሚችል ግልጽነት ወሳኝ ነው ብለዋል።

🟠 በመረጃ ጦርነት ላይ፦ የሱዳን ክስ አሁን ላይ ግጭቶች በውጊያ ሜዳ ብቻ ሳይሆን በመረጃ፣ በሕጋዊ ተቋማት እና በሜዲያ አውታሮች አማካኝነት እንደሚካሄዱ የሚያሳይ የአፍሪካውያንን ሰፊ ሥጋት ያንፀባርቃል።

🟠 በሰብዓዊ መብቶች አጣብቂኝ ላይ፦ የሰብዓዊ መብት አሠራሮች የኃያላን ሀገራት መጠቀሚያ ሆነው ከታዩ ተአማኒነታቸውን ያጣሉ፤ በተቃራኒው ደግሞ ሉዓላዊነት ሁሉንም ነፃ ምርመራዎች ለማገድ ጥቅም ላይ ከዋለ ውጤት አልባ ይሆናሉ።

🟠 የብዝኃ-ዋልታ ፈተናን፦ እውነተኛው ፈተና ሥርዓቱ በብዝኃ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ተአማኒ በሆነ መንገድ መሥራት እና በተለያዩ ግጭቶች እንዲሁም ተዋንያን መካከል ወጥ የሆነ መስፈርት መተግበር መቻሉ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0