በዚምባብዌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ቢያንስ 27 ሰዎች ሕይወታቸው አለፈ

ሰብስክራይብ

በዚምባብዌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ቢያንስ 27 ሰዎች ሕይወታቸው አለፈ

​በማዕከላዊ ዚምባብዌ የሐራሬ-ማስቪንጎ አውራ ጎዳና ላይ ዓርብ ማታ በአውቶቡስ እና በጭነት መኪና መካከል በደረሰው ከባድ ግጭት ከሞቱ ተሳፋሪዎች በተጨማሪ፣ የአምስት ሰዎች ሕይወት በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እና ሌሎች ሁለት ተሳፋሪዎች በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

​የማሾናላንድ ምስራቅ ክልላዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ኢታይ ንዱድዞን ጠቅሰው መገናኛ ብዙኃኑ እንደዘገቡት፣ 23 ሰዎች አደጋው በደረሰበት ቦታ ሲሞቱ፣ አራት ሰዎች ደግሞ በኋላ በሆስፒታል ሕይወታቸው አልፏል።

​የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን፣ ፖሊስ ሁኔታውን ለማጣራት ምርመራ መጀመሩን የአካባቢው ባለሥልጣናት ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0