አፍሪካ የተሰጣት 'የሰንደቅ ዓላማ ነፃነት' እና የይስሙላ ሉዓላዊነት በመሆኑ ቅኝ ግዛት አላበቃም - የታንዛኒያ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

አፍሪካ የተሰጣት 'የሰንደቅ ዓላማ ነፃነት' እና የይስሙላ ሉዓላዊነት በመሆኑ ቅኝ ግዛት አላበቃም - የታንዛኒያ ባለሙያ

"ቅኝ ገዥዎች በወጡበት ወቅት የአፍሪካ ሀገራትን በእውነት ነፃ የማድረግ እውነተኛ ፍላጎት አልነበራቸውም" ሲሉ በሞሮጎሮ ሙስሊም ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ዶ/ር አቡባከር ራጃብ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ባለሙያው ይህን ያሉት አሜሪካ እና ሌሎች የምዕራብ ሀገራት በአፍሪካ ሀገራት የውስጥ ጉዳይ ላይ የሚያደርጉትን ያልተቋረጠ ጣልቃ ገብነት አስመልክተው በሰጡት አስተያየት ነው።

ቅኝ ገዥ ኃይላት የለቀቁት በጥሩ ፈቃድ ሳይሆን በጫና ምክንያት ነው ሲሉ የተከራከሩት ራጃብ፤ የብዝበዛ ሥርዓታቸው ግን እንደቀጠለ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተውበታል።

የቅኝ ግዛት ካባን በኢምፔሪያሊዝም ካባ ማጥለቅ

የኢምፔሪያሊዝም ሥርዓት የአፍሪካን የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ሕይወት መወሰኑን ቀጥሏል ያሉት ራጃብ፤ አፍሪካ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ተይዛ እንድትቆይ የተደረገው የምዕራባውያንን የኢኮኖሚ ውድቀት ለመከላከል ነው ሲሉ አክለዋል።

"እነርሱ [ምዕራባውያን] አካላዊ መሠረታቸውን ከዚህ ያነሱ ቢሆንም፣ ዋና መሥሪያ ቤታቸው ግን እዚያው እንዳለ ነው" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0