ኢትዮጵያ የውሃ ጥራትን በማረጋገጥ የዜጎችን ጤና የሚያስጠብቅ አዲስ ላብራቶሪ ሥራ አስጀመረች
18:25 28.08.2026 (የተሻሻለ: 18:34 28.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የውሃ ጥራትን በማረጋገጥ የዜጎችን ጤና የሚያስጠብቅ አዲስ ላብራቶሪ ሥራ አስጀመረች
የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሀገሪቱን የውሃ ሀብት ጥራትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ ስፔሻላይዝድ የውሃ ጥራት ላብራቶሪ እና ዘርፈ-ብዙ ህንፃዎችን መርቆ ሥራ አስጀምሯል።
የላብራቶሪው አበርክቶ፦
ንጹሕና አስተማማኝ የመጠጥ ውሃ፦ የውሃ ጥራትን በዘመናዊ የላብራቶሪ ቴክኖሎጂ በጥብቅ ለመፈተሽ ስለሚያስችል፣ ማኅበረሰቡ ከውሃ ወለድ በሽታዎች የተጠበቀና አስተማማኝ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኝ ያደርጋል።
የምግብ ደኅንነትና የምርታማነት ዕድገት፦ ለመስኖና ለግብርና የሚውል ውሃ ጥራትን በማረጋገጥ፣ ጤናማና ምርታማ የግብርና ምርት ለሕዝቡ እንዲቀርብ ያስችላል።
ማዕከሉ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ፣ የ3-በ-1 ስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ እና የመዝናኛ ቦታዎችን ያካተተ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X