ሱዳን በቻይና የሚመራ ጎራ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች የልዑካን ቡድን የሥራ ዘመን መራዘምን እንዲያግድ ጠየቀች

ሱዳን በቻይና የሚመራ ጎራ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች የልዑካን ቡድን የሥራ ዘመን መራዘምን እንዲያግድ ጠየቀች
ሀገሪቱ በቻይና የሚመራውና 29 ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ሀገራት ቡድን፤ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በሱዳን ላይ ያቋቋመውን እውነታ አጣሪ የልዑካን ቡድን የሥራ ዘመን ለማደስ የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ እንዲያግድ መጠየቋን የሀገሪቱ የመንግሥት የዜና ኤጀንሲ ሱና ዘግቧል።
ሱዳን አራተኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አሠራር የምትቃወመው ለምንድን ነው
በጄኔቫ የተመድ የሱዳን ቋሚ መልዕክተኛ ሀሰን ሀሚድ ሀሰን እንደገለጹት፤ ከመንግሥት ሙሉ ትብብር ጋር በአሁኑ ወቅት ሦስት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች አካላት በሱዳን ውስጥ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፦
የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሀገር ውስጥ ቢሮ፤
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያ፣
በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ 1591 ስር የተቋቋመ የባለሙያዎች ቡድን።
ቋሚ መልዕክተኛው፤ ለንደን እና ምዕራባውያን ወዳጆቿ ሱዳን ከነባሮቹ ሦስት አካላት ጋር ሙሉ ትብብር እያደረገች ባለችበት ሁኔታ "አራተኛ አሠራር ለመጫን በየዓመቱ የውሳኔ ሃሳብ ረቂቅ ማቅረባቸውን ቀጥለውበታል" ሲሉ ተችተዋል።
አክለውም፤ ረቂቅ የውሳኔ ሃሳቡ የሱዳን ጦርን "የወንጀል ታሪክ ካለውና የዓመፀኞች ቡድን" ከሆነው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር በተሳሳተ መንገድ እኩል አድርጎ ያያል ብለዋል።
ዲፕሎማቱ በስተመጨረሻም፤ የውሳኔ ሃሳቡን ያዘጋጁት አካላት የተመድ ደንቦችን በመጣስ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማንቀሳቀስ የዓመፀኞቹን ትርክት በጦሩ ላይ ለመንዛት እየሠሩ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X