ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኢንቨስተሮች በሀገሪቱ የማዕድን ሀብት መዋዕለ ነዋይ እንዲያፈሱ ጋበዘች

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኢንቨስተሮች በሀገሪቱ የማዕድን ሀብት መዋዕለ ነዋይ እንዲያፈሱ ጋበዘች

 

የሀገሪቱ የወሳኝ እና የኢንዱስትሪ ማዕድናት ዘርፍ አቅም በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በተካሄደው የወሳኝ ማዕድናት ጉባኤ ላይ ቀርቧል።

 

በፕሪቶሪያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተወካይ ደሴ አለባቸው፤ በዘርፉ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለጉባኤው ተሳታፊዎች አቅርበዋል።

 

እንደ ተወካይዋ ማብራሪያ መንግሥት በዘርፉ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ኢንቨስትመንቶች የሚከተሉት ናቸው፦

 

▪ የማዕድናት ፍለጋ፣

▪ ማዕድን ማውጣት፣

▪ እሴት መጨመር፣

▪ የወጡ ማዕድናት ሽያጭ።

 

የኢትዮጵያ ልዑክ ከጉባዔው ጎን ለጎን በሀገሪቱ የማዕድን ሀብት ዕድሎችን ለመቃኘት ፍላጎት ካላቸው ባለሀብቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የትብብር እና የአጋርነት ውይይቶችን እንዳካሄደ በፕሪቶሪያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0