የጤና ሥርዓቶቻችንን እንደገና መቅረጽ አለብን - ዛምቢያዊ የጤና ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የጤና ሥርዓቶቻችንን እንደገና መቅረጽ አለብን - ዛምቢያዊ የጤና ባለሙያ

እንደ አፍሪካ ሲዲሲ እና የአፍሪካ መድኃኒቶች ኤጀንሲ ያሉ ተቋማት በአኅጉሪቱ የጤና ስርዓት ውስጥ ያሉትን ኢኮኖሚያዊ አቅሞች ለመጠቀም የሚያስችሉ ናቸው ሲሉ የዛምቢያ የአንስቴዥዮሎጂስቶች ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ሶምፕዌ ምዋንሳ ከ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

እነዚህ ተቋማት በአኅጉሪቱ ውስጥ መድኃኒቶች እና የሕክምና ቀዶ ጥገና መሣሪያዎች ማምረት የሚቻልበትን ሁኔታ ለማጠናከር ትልቅ አቅም መሆናቸውን ገልጸዋል።

“የጤና ሥርዓቶቻችንን እንደገና መመልከት መጀመር አስፈላጊ ነው። እንደ ማኅበራዊ አገልግሎት ብቻ ማየቱን ትተን፤ እውነተኛ ኢኮኖሚያዊ አቅም እንዳላቸው የሥራ ዘርፎች ልናያቸው ይገባል” ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0