የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ለ50 ሚሊዮን ተቃረበ
21:07 25.08.2026 (የተሻሻለ: 21:14 25.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ለ50 ሚሊዮን ተቃረበ
🪪 እስከ ነሐሴ 18 ድረስ 49.1 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ተነሳሽቱን ተቀላቅለዋል።
ኢትዮጵያዊ 90 ሚሊዮን ዜጎቿን የዚህ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ በማካተት፤ በተመሳሳይ የአግልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ግብ ይዛለች።
ፋይዳ በ2022 ዓ.ም ለሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት የሰባት በመቶ አበርክቶ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ዲጂታል የመታወቂያ (ፋይዳ) ሀገራዊ የዲጂታል መሠረተ ልማትን ወደ ላቀ ሉዓላዊነት እና የኢኮኖሚ ዕድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር ፋይዳቨርስ በሚል እንደገና መቋቋሙ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X