ናሚቢያ ስድስት የነፃነት ጀግኖችን በድጋሚ ቀበረች፤ ደቡብ አፍሪካ በበኩሏ የጠፉ ሰዎችን በማፈላለግ ድጋፍ እንደምታደርግ ቃል ገብታለች - የመንግሥት ሚዲያ

ሰብስክራይብ

ናሚቢያ ስድስት የነፃነት ጀግኖችን በድጋሚ ቀበረች፤ ደቡብ አፍሪካ በበኩሏ የጠፉ ሰዎችን በማፈላለግ ድጋፍ እንደምታደርግ ቃል ገብታለች - የመንግሥት ሚዲያ

የመከላከያ ሚኒስትር አንጀሊና ሞትሼክጋ፤ የጠፉ የነፃነት ታጋዮችን ለማፈላለግ ደቡብ አፍሪካ ከናሚቢያ ጋር ያላትን ጥረት እንደምታድስ አረጋግጠዋል። ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ስድስት አርበኞች ባረፉበት እና ሁለቱ ደግሞ ተምሳሌታዊ መቃብር ባገኙበት የጀግኖች መካነ መቃብር የድጋሚ ቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።

"ዛሬ ለነፃነት ሲሉ ህይወታቸውን የሰጡትን የናሚቢያ ወንድ እና ሴት ልጆችን ወደ ሀገራቸው ለመቀበል በተቀደሰው በጀግኖች መካነ መቃብር ተሰብስበናል። በእርግጥም ጉዟቸው ረጅም፣ የመከራ፣ የመስዋዕትነት እና የፅናት ነበር።"

ደቡብ አፍሪካ የጠፉ ሰዎች እና የእውነትና እርቅ ሂደትን የሚመለከቱ ተነሳሽነቶችን ጨምሮ፤ የዘመዶቻቸውን ሁኔታ አረጋግጠው እልባት ማግኘት ለሚፈልጉ ቤተሰቦች እገዛ ለማድረግ የተለያዩ ኮሚሽኖች እና ተቋማትን ማቋቋሟን ሞትሼክጋ አክለው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
ናሚቢያ ስድስት የነፃነት ጀግኖችን በድጋሚ ቀበረች፤ ደቡብ አፍሪካ በበኩሏ የጠፉ ሰዎችን በማፈላለግ ድጋፍ እንደምታደርግ ቃል ገብታለች - የመንግሥት ሚዲያ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
ናሚቢያ ስድስት የነፃነት ጀግኖችን በድጋሚ ቀበረች፤ ደቡብ አፍሪካ በበኩሏ የጠፉ ሰዎችን በማፈላለግ ድጋፍ እንደምታደርግ ቃል ገብታለች - የመንግሥት ሚዲያ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0