ዓለም አቀፉ የዩሬዥያ ሽልማት ለአፍሪካውያን ክፍት ሆነ
20:13 24.08.2026 (የተሻሻለ: 20:14 24.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዓለም አቀፉ የዩሬዥያ ሽልማት ለአፍሪካውያን ክፍት ሆነ
በአኀጉሪቱ በፈጠራ፣ ማኅበራዊ እና ሰብዓዊ ተነሳሽነቶች ላይ የሚሳተፉ አፍሪካውያን እስከ ነሐሴ 25 ድረስ ማመልከት ይችላሉ።
ሽልማቱን የተመለከቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 10 ዋና ዋና ዘርፎች እና ልዩ ሽልማት፣
🟠 በአጠቃላይ 205 ሺህ ዶላር የሽልማት ገንዘብ፣
🟠 150 በሚበልጡ ባለሙያዎች እና በ50 የዳኞች አባላት ተገምግመው የሚመረጡ 100 ተወዳዳሪዎች፣
🟠 በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከ1,000 በላይ እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እ.ኤ.አ በ2025 በተካሄደው ውድድር ከ27 ሀገራት ከ3,700 በላይ ማመልከቻዎች የቀረቡ ሲሆን ለተወዳዳሪዎች ድጋፍ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ድምፆች ተሰጥተዋል።
ከማመልከቻው የጊዜ ገደብ በኋላ የሚቀጥሉ ቁልፍ የውድድሩ ምዕራፎች፦
1⃣ ከጳጉሜ 2 - መስከረም 17 - የባለሙያዎች ግምገማ፣
2⃣ ከመስከረም 25 - ጥቅምት 3 - ክፍት ዓለም አቀፍ ድምፅ አሰጣጥ፣
3⃣ ከጥቅምት 3-5 — የፕሮጀክት ማብራሪያ ለዳኞች ማቅረብ፣
4⃣ ጥቅምት 5 - የአሸናፊዎች የሽልማት ሥነ-ሥርዓት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X