በሩሲያ አሸማጋይነት ከ1,400 በላይ የማዕከላዊ አፍሪካ ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ

© telegram sputnik_ethiopiaበሩሲያ አሸማጋይነት ከ1,400 በላይ የማዕከላዊ አፍሪካ ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ
በሩሲያ አሸማጋይነት ከ1,400 በላይ የማዕከላዊ አፍሪካ ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.08.2026
ሰብስክራይብ

በሩሲያ አሸማጋይነት ከ1,400 በላይ የማዕከላዊ አፍሪካ ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ

እጃቸውን ከሰጡት ታጣቂዎች ውስጥ 932ቱ በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም ውስጥ ተሳትፈዋል ሲሉ የዓለም የደህንነት መኮንኖች ሕብረትን ጠቅሰው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ፕሬዚዳንት አርካንጀ ቱዋዴራ እ.ኤ.አ በ2019 የታዩ አስተዳደራዊ መዘግየቶች እንዲቀረፉ በጠየቁት መሠረት፤ የሩሲያ አሠልጣኞች የ "3አር" እና "ዩፑሲ" ቡድኖችን ትጥቅ የማስፈታት ኃላፊነት መረከባቸውን ድርጅቱ በሪፖርቱ ገልጿል።

ሩሲያውያኑ አሠልጣኞች በተጨማሪም፦

ከሁሉም አዛዦች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት መስርተዋል፣

እ.ኤ.አ በ2019 የተዘረጉትን የቡድን አዛዦች የመገናኛ መስመሮች እንደገና ሥራ አስጀምረዋል፣

የሎጂስቲክ ድጋፍ እና ቀጥተኛ ቅንጅት ፈጥረዋል።

ℹ ሂደቱ እ.ኤ.አ በ2019 የካርቱም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የተመድ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ እና በምዕራባውያን መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ቢሮክራሲያዊ አሠራር ምክንያት ዘግይቶ እንደነበር ድርጅቱ ጠቁሟል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0