የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት እና ኤ23 አማፂያን በሰላም ፍኖተ–ካርታ ላይ ተስማሙ – መግለጫ
08:58 24.08.2026 (የተሻሻለ: 09:04 24.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት እና ኤ23 አማፂያን በሰላም ፍኖተ–ካርታ ላይ ተስማሙ – መግለጫ
በኳታር፣ በአሜሪካ፣ በቶጎ፣ በስዊዘርላንድ እና በአፍሪካ ሕብረት አደራዳሪነት በጄኔቫ ለ5 ቀናት ከተካሄደው ድርድር በኋላ፣ ቀደም ሲል የተደረሱትን የሰላም ስምምነቶች ለመተግበር የሚያስችል ፍኖተ–ካርታ መዘጋጀቱን የጋራ መግለጫው አመላክቷል።
በወገኖቹ የተደረሱ ዋና ዋና ስምምነቶች፦
🟠 በዶሃ ማዕቀፍ ሥር ለሚደረጉ ድርድሮች የተዘጋጁ ቅደም ተከተሎች እና የጊዜ ሰሌዳዎች፣
🟠 የለውጥ ሂደቶችን ለመገምገም እና የአፈጻጸም ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል አሰራር፣
🟠 በምስራቃዊ ዲአርሲ ሚኔምብዌ ለሰኞ የተያዘው የመጀመሪያው የተኩስ ማቆም ማረጋገጫ ተልዕኮ፣ ከጥሰቶች ሪፖርት ማድረጊያ መደበኛ ዘዴ ጋር እንዲሁም
🟠 ወደ አጠቃላይ ሰላም እና የግጭት አፈታት የሚያመሩ ድርድሮችን ለመቀጠል የተገባ ቁርጠኝነት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X