ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን የወተት ምርት በሀገር ውስጥ ምርት መተካት የሚያስችል ብሔራዊ ፍኖተ-ካርታ ልታዘጋጅ ነው
19:24 23.08.2026 (የተሻሻለ: 19:34 23.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን የወተት ምርት በሀገር ውስጥ ምርት መተካት የሚያስችል ብሔራዊ ፍኖተ-ካርታ ልታዘጋጅ ነው
ፍኖተ-ካርታው በግብርና ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና በኔዘርላንድ የልማት ድርጅት "ብሪጅ ፕላስ" ፕሮጀክት ትብብር እየተዘጋጀ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።
ብሔራዊ ፍኖተ-ካርታው የሚከተሉትን ተሞክሮዎች ለወተት ላም አርቢዎች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው።
🟠 የቴክኖሎጂ፣
🟠 የገበያ ትስስር እና
🟠 በአቅም ግንባታ
"ብሪጅ ፕላስ" ፕሮጀክት ፕሮጀክት እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት የነጠላ ላም የቀን የወተት ምርትን በአማካይ በ3.8 ሊትር ማሳደግ ተችሏል። ይህን ስኬት አጠናክሮ ለማስቀጠልም በ5 ዓመታት የምርት ዘመን "ላም-ተኮር የምክር አገልግሎትን" ለ350 ሺህ አርሶ እና አርብቶ አደሮች ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X