አሜሪካ በሕገ-ወጥ መንገድ የወጡ 48 ቅርሶችን ለግብፅ መልሳ አስረከበች

ሰብስክራይብ

አሜሪካ በሕገ-ወጥ መንገድ የወጡ 48 ቅርሶችን ለግብፅ መልሳ አስረከበች

በኤፍ.ቢ.አይ የሎስ አንጀለስ ቢሮ ርክክብ የተደረገባቸው እነዚህ ቅርሶች የፈርዖን፣ የሮማውያን እና የኮፕቲክ ዘመናት የነበሩ ጌጣጌጦችን፣ ሐውልቶችን፣ እምነታዊ ክታቦችን እና የቀብር ሥነ-ሥርዓት ቁሳቁሶችን የሚያካተቱ መሆናቸውን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

የአፍሪካ ሀገራት የተዘረፉ የባህል ቅርስ ሀብቶቻቸውን ለማስመለስ የሚያደርጉትን ጥረት ቀጥለዋል። እ.ኤ.አ. በ2016 ከተፈረመው የሁለትዮሽ ስምምነት ወዲህ አሜሪካ ከ5,000 በላይ ቅርሶችን ለግብፅ መመለሷን ዘገባዎች ያመለክታሉ።

ቅርሶቹ የተያዙት የመጨረሻው የቅርሶቹ ባለቤት በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን በፈቃደኝነት ጥቆማ ካደረጉ በኋላ ነው። ዋናው የቅርሶች ሕገ-ወጥ አዛዋሪ የሞተ ቢሆንም፣ ሊኖሩ የሚችሉ ተባባሪዎችን ለመለየት እና ሌሎች የተበተኑ ቁሳቁሶችን ለማግኘት ምርመራው ቀጥሏል።

ሩሲያም የአፍሪካን የባህል ቅርሶች የመመለስ ጥረቶችን ደግፋለች። የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩድዜቶ አብላክዋ የአፍሪካ ቅርሶችን ለማስመለስ የሚደረጉ ጥረቶችን በመደገፏ ሞስኮን በቅርቡ አመስግነዋል።

በመጪው መስከረም ወር የጋናው ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ በ81ኛው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን የባህል ቅርሶችን በማስመለስ ላይ የሚያተኩር ጉባኤ ያስተናግዳሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0