ፑቲን እና ትራምፕ በቻይና የእስያ-ፓስፊክ የኢኮኖሚ ትብብር ጉባኤ ከተሳተፉ መገናኘታቸው "የማይቀር ነው" - የክሬምሊን ረዳት
15:29 23.08.2026 (የተሻሻለ: 15:34 23.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፑቲን እና ትራምፕ በቻይና የእስያ-ፓስፊክ የኢኮኖሚ ትብብር ጉባኤ ከተሳተፉ መገናኘታቸው "የማይቀር ነው" - የክሬምሊን ረዳት
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካ አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ በመጪው ኅዳር በቻይና በሚካሄደው የእስያ-ፓስፊክ የኢኮኖሚ ትብብር ጉባኤ ጎን ለጎን፣ ተገናኝተው ውይይት ሊያደርጉ እንደሚችሉ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ተናግረዋል።
ጉባኤው ኅዳር 18-19 በቻይና ሼንዘን ከተማ ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ስብሰባው ንግድን፣ ኢንቨስትመንትን እና የንዑስ ክልል ውህደትን ለመወያየት ከ21 ኢኮኖሚዎች የተውጣጡ መሪዎችን ያሰባስባል።
በፑቲን እና በትራምፕ መካከል የተደረገው የመጨረሻው የገጽ ለገጽ ስብሰባ እ.አ.አ ነሐሴ 15 ቀን 2025 በአላስካ አንኮሬጅ የተካሄደ መሆኑ ይታወሳል። ሁለቱም ወገኖች ንግግሮቹን "ገንቢ" ሲሉ የገለጿቸው ሲሆን፣ በሁለትዮሽ ግንኙነቶች፣ ስትራቴጂካዊ መረጋጋት እና በዩክሬን ያለው ሁኔታ ላይ መክረውበታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X