አዲስ አበባ መንገዶቿን ከማያልቅ ቁፋሮ የሚታደግ አዲስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረች
18:24 22.08.2026 (የተሻሻለ: 18:34 22.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አዲስ አበባ መንገዶቿን ከማያልቅ ቁፋሮ የሚታደግ አዲስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረች
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን የከተማዋን የትራፊክ እንቅስቃሴና የንግድ ክዋኔ ሳይስተጉል ከመሬት በታች የፍሳሽ መስመሮችን የሚዘረጋበትን "ማይክሮ ተነሊንግ" ቴክኖሎጂ ትግበራ ተጀምሯል።
ቴክኖሎጂው መንገዶችንና የመሠረተ ልማት አውታሮችን ሳይቆፍሩ ከመሬት በታች ብቻ በመቦርቦር የፍሳሽ ትቦዎችን ለማሳለፍ የሚያስችል ነው።
የተከናወኑ ዋና ዋና የፕሮጀክት ሥራዎች፦
🟠 በመገናኛ (ደራርቱ ሕንፃ አቅራቢያ) 55 ሜትር የባቡር ሐዲድና የአስፓልት መንገድ የሚያቋርጥ የፍሳሽ መስመር ዝርጋታ፤
🟠 ከሲኤምሲ ወደ አዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል፦ 92 ሜትር ርዝመት ያለው የመሬት ውስጥ መቦርቦር ሥራ፤
🟠 የቱቦ መጠን፦ በሁለቱም ሳይቶች 600 ሚሊ ሜትር ዲያሜትር ቱቦዎች ዝርጋታ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ ሥራ የምስራቅ ተፋሰስ የፍሳሽ መሠረተ ልማት ማሻሻያ ፕሮጀክት አካል ሲሆን፤ የትራፊክ መጨናነቅን እና የመሠረተ ልማት ውድመትን በመቀነስ የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓቱን እንደሚያዘምን የከተማ አስተዳደሩ ገልጿል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/4
© telegram sputnik_ethiopia

2/4
© telegram sputnik_ethiopia

3/4
© telegram sputnik_ethiopia

4/4
© telegram sputnik_ethiopia
1/4
© telegram sputnik_ethiopia
2/4
© telegram sputnik_ethiopia
3/4
© telegram sputnik_ethiopia
4/4
© telegram sputnik_ethiopia