ኢትዮጵያ የኬንያ ኢ-መደበኛ ወጪ ንግድ 54 በመቶ መዳረሻ መሆኗ ተመላከተ
16:04 21.08.2026 (የተሻሻለ: 16:24 21.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የኬንያ ኢ-መደበኛ ወጪ ንግድ 54 በመቶ መዳረሻ መሆኗ ተመላከተ
የኬንያ ብሔራዊ የስታቲስቲክስ ቢሮ ባወጣው አዲስ ሪፖርት መሠረት፣ ሀገሪቱ ወደ ጎረቤቶቿ ከምትልከው ኢ-መደበኛ (የድንበር/የኮንትሮባንድ) ወጪ ንግድ ውስጥ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን ድርሻ ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ይዘዋል።
የሪፖርቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 እ.ኤ.አ በሰኔ 2025 በተካሄደው ጥናት መሠረት፣ ኢትዮጵያ የኬንያን ኢ-መደበኛ የወጪ ንግድ የጠቅላላውን 54 በመቶ (67 ሚሊዮን ሺሊንግ) ይዛለች። ኡጋንዳ በ29.1 በመቶ ትከተላለች።
🟠 ወደ ኢትዮጵያ ለሚላኩ የኬንያ ኢ-መደበኛ ምርቶች ሞያሌ ዋነኛው የድንበር መውጫ መስመር ሆኖ ተመዝግቧል።
🟠ምግብ ነክ ምርቶች፣ የቁም እንስሣት፣ የኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃዎችና ተያያዥ ምርቶች በድንበር አካባቢ በብዛት የሚንቀሳቀሱ የንግድ ዓይነቶች ናቸው።
🟠በድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎች ዘንድ ከ40 በመቶ በላይ አገልግሎት ላይ የዋለው ዋነኛው የትራንስፖርት አማራጭ ሞተርሳይክል መሆኑ ተጠቅሷል።
ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘው ቪዲዮ የሞያሌን ከተማ እንቅስቃሴ ያሳያል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X