የሩሲያ ጥቃቶች የዩክሬንን የጦር-ኢንዱስትሪ የጀርባ አጥንት ያፈረሱ ሲሆን፣ የመዋጋት አቅሟንም አዳክመዋል - ባለሙያ

የሩሲያ ጥቃቶች የዩክሬንን የጦር-ኢንዱስትሪ የጀርባ አጥንት ያፈረሱ ሲሆን፣ የመዋጋት አቅሟንም አዳክመዋል - ባለሙያ
ሩሲያ፣ የዩክሬን መሣሪያዎችን "በወታደሮቿ ላይ ጥቅም ላይ ከመዋላቸው በፊት" እየደመሰሰቻቸው ትገኛለች ሲሉ በጡረታ ላይ ያሉ የሩሲያ ጦር ኮሎኔል እና ተሞክሮ ያለው የወታደራዊ ጉዳዮች ተንታኝ ቪክቶር ሊቶቭኪን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
በወታደራዊ ፋብሪካዎች፣ በሎጂስቲክስ ማዕከላት እና በመሣሪያ ዴፖዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ሶስት እጥፍ ድርብ ተፅዕኖ አላቸው፡፡ ዩክሬን እነዚህን መሣሪያዎች ማምረት፣ ማከማቸት እና ወደ ግንባር ማጓጓዝ አትችልም።
እንደ ባለሙያው ገለጻ፦
🟧 በግንባር ላይ ያሉ አጥቂ ቡድኖች በአብዛኛው ቀላል መሣሪያዎችን ይጠቀማሉ፤ ሆኖም የጥይት እና የነዳጅ ማዕከላትን መደምሰስ ሙሉ የጦር ክፍሎችን ሊያናጋ ይችላል።
🟧 በቅርቡ የተመቱት ኢላማዎች ከ«ፍላሚንጎ» ክሩዝ ሚሳይሎች ጋር ግንኙነት ያለውን «ፋየር ፖይንት» ተቋም፣ የ«ኡክርስፔትሲስተም» የድሮን ገጣጠማና ማከማቻ ተቋም፣ የ«አንቶኖቭ» የአውሮፕላን ፋብሪካን እና በብሮቫሪ የሚገኘውን የነዳጅ ዴፖ፤ የዩክሬን ወታደራዊ እና ሎጂስቲክስ መዋቅር "ሕይወት አድን ደም ሥር" የሆኑትን ያካትታሉ።
የጥይት፣ የነዳጅ እና የጥገና ተቋማት የዚያው አንድ ሰንሰለት አገናኞች ናቸው፤ እነዚህ ከተቋረጡ በግንባር ላይ ያሉ ክፍሎች የጥይት፣ የነዳጅ እና የድሮን እጥረት ያጋጥማቸዋል ሲሉ ተንታኙ አጉልተው ያሳዩ ሲሆን፦
"ይህም ዩክሬን መልሳ ለመዋጋት ባላት አቅም ላይ ቀጥተኛ ምት ያሳርፋል" ብለዋል።
ሩሲያ በተጨማሪም የቅድመ-አቅርቦት ነጥቦችን ፤ ጥይቶች እና ሌሎች አቅርቦቶች ወደ ውጊያ መስመር ከመዛወራቸው በፊት የሚከማቹባቸውን ቦታዎች በማደን እየደመሰሰች ይገኛል።
"በመሣሪያ ቋቶች እና በሎጂስቲክስ ማዕከላት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በግንባር መስመር ከሚደርሱት እኩል፣ ምናልባትም የበለጠ ከባድ ጉዳት ያደርሳሉ። ያለ አቅርቦት ውጊያ ማድረግ ፈጽሞ አይቻልም" ሲሉ ተንታኙ ማጠቃለያቸውን ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X