ሩሲያ የ3ኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ አጀንዳ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለማተኮር አቅዳለች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

© telegram sputnik_ethiopiaሩሲያ የ3ኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ አጀንዳ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለማተኮር አቅዳለች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
ሩሲያ የ3ኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ አጀንዳ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለማተኮር አቅዳለች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.08.2026
ሰብስክራይብ

ሩሲያ የ3ኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ አጀንዳ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለማተኮር አቅዳለች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

ሞስኮ ለ3ኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ በንቃት ዝግጅት እያደረገች መሆኑን ማሪያ ዛካሮቫ ገልጸዋል።

ዛካሮቫ በሰጡት መግለጫ፣ "በሞስኮ ለሚካሄደው 3ኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ በአሁኑ ወቅት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል። የንግድ እና የኢንቨስትመንት ትብብራችንን ለማስፋፋት ያለንን የጋራ ፍላጎት ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የመጪውን ከፍተኛ ደረጃ ስብሰባ አጀንዳ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለማተኮር አቅደናል" ብለዋል።

የሁሉም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እና የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም የአኅጉሪቱ ቀጣናዊ የትብብር ድርጅቶች የሥራ አስፈፃሚ አካላት ኃላፊዎች ጥሪ ተደርጎላቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።

ሩሲያ እና የአፍሪካ ሀገራት ለኢኮኖሚ ትብብር የሚሆን ከፍተኛ ያልተጠቀሙበት አቅም እንዳላቸው ቃል አቀባይዋ አክለው ገልጸዋል።

3ኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ጥቅምት 18 እና 19 በሞስኮ ይካሄዳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0