አምስት የአፍሪካ ሀገራት ከጥብቅ ግምገማዎች በኋላ የፖሊዮ ወረርሽኝ ማብቃቱን አበሰሩ - የዓለም ጤና ድርጅት

© telegram sputnik_ethiopiaአምስት የአፍሪካ ሀገራት ከጥብቅ ግምገማዎች በኋላ የፖሊዮ ወረርሽኝ ማብቃቱን አበሰሩ - የዓለም ጤና ድርጅት
አምስት የአፍሪካ ሀገራት ከጥብቅ ግምገማዎች በኋላ የፖሊዮ ወረርሽኝ ማብቃቱን አበሰሩ - የዓለም ጤና ድርጅት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.08.2026
ሰብስክራይብ

አምስት የአፍሪካ ሀገራት ከጥብቅ ግምገማዎች በኋላ የፖሊዮ ወረርሽኝ ማብቃቱን አበሰሩ - የዓለም ጤና ድርጅት

ቡሩንዲ፣ ጋና፣ ጊኒ-ቢሳው፣ ኮንጎ ሪፐብሊክ እና ኡጋንዳ ከጥር እስከ ሰኔ ባለው ጊዜ ውስጥ የተካሄዱ የተናጥል ግምገማዎችን ተከተሎ የፖሊዮ ቫይረስ አይነት 2 ስርጭትን በተሳካ ሁኔታ ማስቆማቸውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት አረጋግጧል።

ወረርሽኞቹ ማብቃታቸው የታወጀው የበሽታ ቅኝት፣ የላቦራቶሪ እና የኤፒደሚዮሎጂ መረጃዎች ከተገመገሙ በኋላ ነው።

ለስኬቱ ምክንያቶች፦

🟠 ጠንካራ ሀገራዊ አመራር፣

🟠 ቁርጠኛ የጤና ባለሙያዎች፣

🟠 ፈጣን የመለየት ሂደት፣

🟠 የማህበረሰብ ተሳትፎ እና

🟠 ጥራት ያላቸው የክትባት ዘመቻዎች።

"የእነዚህ ወረርሽኞች ማብቃት ምን ያህል ውጤት ማሳካት እንደሚቻል ማሳያ ነው" ያሉት የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ዳይሬክተር ዶ/ር ሞሐመድ ጃናቢ፣ "ሆኖም ቀጣይነት ያለው ጥንቃቄ፣ ጠንካራ ቅኝት እና ከፍተኛ የክትባት ሽፋን አሁንም ወሳኝ ናቸው" ሲሉ አሳስበዋል።

ቀደም ሲል ወረርሽኝ ማብቃቱ ከተወጀ በኋላ በቅርቡ በማዳጋስካር እንደታየው ሁሉ፣ በሽታው ዳግም ከሌሎች ሀገራት የመግባት ስጋቱ አሁንም እንዳለ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0