የቻይና ኩባንያዎች በ12.5 ቢሊዮን ዶላሩ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ የበላይነቱን ያዙ
18:15 20.08.2026 (የተሻሻለ: 18:24 20.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቻይና ኩባንያዎች በ12.5 ቢሊዮን ዶላሩ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ የበላይነቱን ያዙ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ የቅድመ-ማጣሪያ ደረጃን ያለፉ ኩባንያዎችን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ የቻይና ኩባንያዎች በዝርዝሩ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል።
ቁልፍ ነጥቦች፦
🟠 በቅድመ-ማጣሪያው ከተለዩት 33 እጩዎች መካከል 15ቱን (45.5%) የቻይና መንግሥት ይዞታ ያላቸውና አጋር ኩባንያዎች ተቆጣጥረውታል፡፡
🟠 ከቻይና በተጨማሪ የቱርክ፣ ጣሊያን፣ ፈረንሳይ፣ ኳታር፣ ደቡብ ኮሪያ፣ አሜሪካ፣ ፖርቱጋል፣ ሩሲያ፣ ሕንድ እና የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ኩባንያዎች በቅድመ-ማጣሪያው ተካተዋል።
🟠 ተወዳዳሪዎች የፋይናንስና የቴክኒክ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ በተጠየቀው መሠረት የመጨረሻው አሸናፊ ኩባንያ ምርጫ ማሳወቂያ እስከ ጥር 2019 ዓ.ም መራዘሙ ተገልጿል።
የቻይና ኩባንያዎች የሲቪል ግንባታ ክፍሎችን በመምራት ላይ ሲሆኑ፣ አሜሪካ በበኩሏ በአቪዬሽን ቴክኖሎጂ፣ የመሣሪያዎች አቅርቦት እና በቦይንግ አውሮፕላኖች ግዥ በኩል በፕሮጀክቱ ውስጥ ድርሻ ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X