በመቶዎች የሚቆጠሩ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች ከሱዳን ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፤ ለዓመፀኛው ከፊል ወታደራዊ ኃይል ትልቅ ኪሳራ ሆነ

ሰብስክራይብ

በመቶዎች የሚቆጠሩ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች ከሱዳን ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፤ ለዓመፀኛው ከፊል ወታደራዊ ኃይል ትልቅ ኪሳራ ሆነ

▫ በሰሜናዊ ግዛት የምትገኘው አል-ዳባህ ከነሙሉ ትጥቁ የከዳውን ኃይል ረቡዕ ዕለት የተቀበለች ሲሆን፣ የሱዳን ድንበር ጠባቂ አዛዥ ኮሎኔል መሐመድ ሳላህ ዩኒስ ቡድኑን በይፋ ተቀብለው "ወደ እናት ሀገር ለመመለስ" ያደረጉትን ውሳኔ አድንቀዋል።

ዋና ዋና ዝርዝሮች፦

የከዳው ኃይል፦ 'ሙሳ ኻምሲን' በመባል የሚታወቁት ብሪጋዴር ሙሳ አሊ አህመድ ከ318 ተዋጊዎች እና ከ50 የውጊያ ተሽከርካሪዎች ጋር ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን በመክዳት የሱዳን ጦር ኃይሎችን ተቀላቅለዋል።

የክዳቱ ምክንያት፦ ኻምሲን በአማፂ ቡድኑ ውስጥ የተቋማዊ አሰራር አለመኖርን እና ለ'ብሔራዊ አንድነት' ያላቸውን ቁርጠኝነት በምክንያትነት ጠቅሰዋል።

የሠራዊቱ አቀባበል፦ ኮሎኔል ዩኒስ "ወደ ሠራዊቱ ሰልፍ ለመመለስ ለሚፈልጉ ሁሉ የሀገር ደጅ ክፍት እንደሆነ ይቆያል" ሲሉ ያረጋገጡ ሲሆን፣ ሁሉም ሱዳናውያን የቅጥር ተዋጊዎችን ተፅዕኖ እንዲመክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

© telegram sputnik_ethiopia
በመቶዎች የሚቆጠሩ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች ከሱዳን ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፤ ለዓመፀኛው ከፊል ወታደራዊ ኃይል ትልቅ ኪሳራ ሆነ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
በመቶዎች የሚቆጠሩ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎች ከሱዳን ሠራዊት ጋር ተቀላቀሉ፤ ለዓመፀኛው ከፊል ወታደራዊ ኃይል ትልቅ ኪሳራ ሆነ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0