የሕግ ሥርዓትን ከቅኝ ግዛት ተፅዕኖ ነፃ ማድረግ፦ የአፍሪካ ሀገራት የሀገር በቀል ሕጎችን ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች ጋር ማጣመር ለምን ያስፈልጋቸዋል? - የናይጄሪያ ባለሙያ ማብራሪያ
የሕግ ሥርዓትን ከቅኝ ግዛት ተፅዕኖ ነፃ ማድረግ፦ የአፍሪካ ሀገራት የሀገር በቀል ሕጎችን ከዓለም አቀፍ መስፈርቶች ጋር ማጣመር ለምን ያስፈልጋቸዋል? - የናይጄሪያ ባለሙያ ማብራሪያ
እውነተኛ ሉዓላዊነት ከፖለቲካዊ ነፃነት በላይ ብዙ ነገርን ይጠይቃል፤ ይህም በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገርን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ የሚያስችል የሕግ አቅምን ይጠይቃል ሲሉ በናይጄሪያ የሕግ ተቋም ውስጥ በተግባር ልምምድ ላይ የሚገኙት ሻሮን አጉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የፍትሕ ሥርዓትን ከቅኝ ግዛት ተፅዕኖ ነፃ ማድረግ ማለት ጥብቅ የሆኑ አሰራሮችን ሙሉ በሙሉ መተካት ሳይሆን፣ የጋራ ሕግን ከሀገር በቀል የማስታረቂያ የፍትሕ ሞዴሎች ጋር ማጣመር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
"የባህል መርሆች ከሕገ-መንግሥቱ እና ከመሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ጋር የሚጣጣሙ በሚሆኑበት ጊዜ፣ ሀገር በቀል ስለሆኑ ብቻ እንደ ዝቅተኛ ተደርገው ሊወሰዱ አይገባም" ሲሉ በጉልህ አንስተዋል።
ይህንን ለማብራራትም፣ ባህላዊ ሥነ-ምግባርን የሚመራውን እና በታሪክ የህብረተሰቡን በርካታ የሕይወት ዘርፎች እርቅንና ስምምነትን በመመለስ ሲያስተዳድር የቆየውን የኢግቦ ሕዝብ የ"ኦሜናላ"* መርሕ አጉልተው አሳይተዋል። በአንጻሩ፣ የምዕራባውያን የፍትሕ ሥርዓቶች ብዙ ጊዜ 'እጅግ አስጨናቂ' ሊሆኑ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
በስተመጨረሻም፣ የአፍሪካ ሀገራት ውስብስብ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ለመደራደር እና ኢኮኖሚያቸውን እኩልነት የጎደላቸው ከሆኑ የውጭ ሀገራት አጋርነቶች ለመጠበቅ ጠንካራ ተቋማት እና የሙያ ብቃት ያላቸው የሕግ ባለሙያዎች ያስፈልጓቸዋል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
*ℹ ኦሜናላ የማኅበረሰብ ሕይወትን፣ ፍትሕን እና ሥነ-ምግባርን የሚመራ የኢግቦ ሕዝብ ባህላዊ ሞራል፣ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ሕግ ነው። ተግባራዊ፣ ተለዋዋጭ እና በሕብረተሰብ መሪዎች የሚጠበቅ ሲሆን፣ ዋና ዋና እሴቶቹ በሕይወት፣ በትውልድ፣ በሀብት፣ በሰላም እና በፍቅር ላይ ያተኮሩ ናቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X