ምዕራባውያን እና የነዳጅ ኩባንያዎቻቸው "የአፍሪካን አቅም አቅልለው ይመለከቱታል" - የቀድሞው የኒጀር ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

ምዕራባውያን እና የነዳጅ ኩባንያዎቻቸው "የአፍሪካን አቅም አቅልለው ይመለከቱታል" - የቀድሞው የኒጀር ሚኒስትር

አፍሪካ ከዓለም አቀፉ የነዳጅ አቅም ከ12 እስከ 13 በመቶ የሚሆነውን የምትይዝ ሲሆን፣ እንደ አንድ አምራች ተቆጥራ ቢሆን ኖሮ ታላላቅ ኃያላን ሀገራትን መገዳደር ትችል ነበር ሲሉ ሀገራዊ ደህንነት መጠበቂያ ብሔራዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አማካሪ ማሃማን ላዋን ጋያ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"በእውነተኛ ትብብር፣ በተለይም ከብሪክስ፣ ከሩሲያ እና ከቻይና ጋር በሚደረግ ትብብር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፉ የነዳጅ እና የኃይል መስክ ተገቢ ቦታዋን ታገኛለች ብዬ እምናለሁ። አሁን ያለነው በአዲሱ የዓለም ኢኮኖሚ ስርዓት ምዕራፍ ውስጥ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

የነዳጅ ሀብቶች ከእንግዲህ እንደ ጥሬ ዕቃ መሸጥ የለባቸውም፤ አፍሪካም በእሴት ጭማሪ ላይ ትኩረት ማድረግ አለባት ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

እንደ ጋያ ገለጻ፣ ለረጅም ጊዜ ወደ ፈረንሳይ ሲላክ ለቆየው የኒጀር ዩራኒየምም ተመሳሳይ አሰራር ሊተገበር ይገባል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0