ደቡብ አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ከሕንድ ጋር ከፍተኛ የኮምጣጣ ፍራፍሬዎች ወጪ ንግድ ስምምነት ተፈራረመች

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ በአውሮፓ ገበያ ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ከሕንድ ጋር ከፍተኛ የኮምጣጣ ፍራፍሬዎች ወጪ ንግድ ስምምነት ተፈራረመች

ለአስር ዓመታት ያህል ከተካሄደ ድርድር በኋላ ሕንድ ለፍራፍሬ ዝንብ መከላከያ የሚያገለግሉ የቀዝቀዛ አያያዝ አማራጮችን ማፅደቋን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ አስታውቋል። ይህም የተሻለ የሎጂስቲክ ሁኔታን ከመፍጠሩ ባሻገር የደቡብ አፍሪካን የኮምጣጣ ፍራፍሬዎች ጥራት ለማሻሻል ይረዳል።

ይህ ስኬት ዘርፉ ከአውሮፓ ውጭ ተጨማሪ ገበያዎችን ለማስፋፋት እና የሕንድን 1.47 ቢሊዮን ገበያ ለመጠቀም የሚያደርገውን ጥረት እንደሚደግፍ ባለሥልጣናት ጠቁመዋል።

የደቡብ አፍሪካ የግብርና ሚኒስትር ዊሊ ኦካምፕ፤ የንግድ ማነቆዎችን ለመቅረፍ የላቀ የግብርና ቴክኖሎጂ የተጫወተውን ሚና አድንቀዋል።

 

"ይህ የሚያሳየው ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የደቡብ አፍሪካ አርሶ አደሮች የንግድ ዕክሎችን በማለፍ ሌሎች ሀገራት በከፍተኛ ጥራት የተመረቱ ምርቶቻችንን እንዲቀምሱ ማስቻላቸውን ነው" ብለዋል።

 እ.ኤ.አ በ2025 ደቡብ አፍሪካ 3.2 ሚሊዮን ቶን ሲትረስ ወደ ውጭ በመላክ፤ ስፔንን በልጣ በዓለም አንደኛ ደረጃን ይዛለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0