በምዕራብ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የወርቅ ማዕድን ማውጫ ተንዶ በትንሹ የ30 ሰዎች ሕይወት አለፈ
17:03 19.08.2026 (የተሻሻለ: 17:04 19.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በምዕራብ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የወርቅ ማዕድን ማውጫ ተንዶ በትንሹ የ30 ሰዎች ሕይወት አለፈ
ባለሥልጣናት ማክሰኞ ስለደረሰው አደጋ ያወጡት የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ፡-
▪ ከተናደው ጉድጓድ ውስጥ የ30 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል፣
▪ በርካታ የተጎዱ የማዕድን ሠራተኞች የሕክምና እርዳታ በማግኘት ላይ ይገኛሉ፣
▪ ሌሎች ተጎጂዎች አሁንም ከመሬት በታች ተቀብረው እንዳሉ ናቸው።
የመንግሥት ቃል አቀባይ ኤቫሪስት ንጋማና ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል።
ባለሥልጣናት ለተጎዱት ወገኖች "እርዳታና ድጋፍ ለማቅረብ ሳይታክቱ እየሠሩ ይገኛሉ" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X