ቤኒናዊቷ ድምፃዊት በሆሊዉድ የዝነኞች ንጣፍ ኮከብ የተቀዳጀች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሙዚቀኛ ሆነች
16:11 19.08.2026 (የተሻሻለ: 16:14 19.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቤኒናዊቷ ድምፃዊት በሆሊዉድ የዝነኞች ንጣፍ ኮከብ የተቀዳጀች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሙዚቀኛ ሆነች
የአምስት ጊዜ የግራሚ አሸናፊዋ አንጄሊክ ኪድጆ፤ ማክሰኞ በካሊፎርኒያ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት በሆሊዉድ ዎልክ ኦፍ ፌም ስሟን እና የእጇን አሻር አኑራለች።
ታሪካዊ የሙዚቃ ሕይወት፦ ኪድጆ ከ40 ዓመታት በላይ በዘለቀ እና 18 አልበሞችን ባካተተው የሙዚቃ ሕይወቷ፤ ባሕላዊ ዜማዎችን ከጃዝ፣ ፈንክ እና ፖፕ ጋር በማዋሃድ የአፍሪካን ድምፅ ለዓለም አቀፍ አዳማጮች አቅርባለች። ይህ ተፅዕኖዋ በዓለም ዙሪያ ከሚከበሩ እና አነቃቂ ከሆኑ ድምፃውያን አንዷ አድርጓታል።
ከሙዚቃ ባሻገር፦ ኪድጆ ከመድረክ ባለፈ ባቋቋመችው 'ባቶንጋ' ፋውንዴሽን አማካኝነት በመላው አፍሪካ የሚገኙ ሴቶች እና ወጣቶችን ታበቃለች። በተጨማሪም ለአዲሱ ትውልድ የአፍሪካ ከዋክብት መነሳሳትን በመፍጠር፤ በባሕል የበለፀጉ የአኀጉሪቱ የሙዚቃ ሀብቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ጎልተው እንዲወጡ በማድረግ ላይ ትገኛለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X