ቤኒናዊቷ ድምፃዊት በሆሊዉድ የዝነኞች ንጣፍ ኮከብ የተቀዳጀች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሙዚቀኛ ሆነች

ሰብስክራይብ

ቤኒናዊቷ ድምፃዊት በሆሊዉድ የዝነኞች ንጣፍ ኮከብ የተቀዳጀች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሙዚቀኛ ሆነች

​ የአምስት ጊዜ የግራሚ አሸናፊዋ አንጄሊክ ኪድጆ፤ ማክሰኞ በካሊፎርኒያ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት በሆሊዉድ ዎልክ ኦፍ ፌም ስሟን እና የእጇን አሻር አኑራለች።

ታሪካዊ የሙዚቃ ሕይወት፦ ኪድጆ ከ40 ዓመታት በላይ በዘለቀ እና 18 አልበሞችን ባካተተው የሙዚቃ ሕይወቷ፤ ባሕላዊ ዜማዎችን ከጃዝ፣ ፈንክ እና ፖፕ ጋር በማዋሃድ የአፍሪካን ድምፅ ለዓለም አቀፍ አዳማጮች አቅርባለች። ይህ ተፅዕኖዋ በዓለም ዙሪያ ከሚከበሩ እና አነቃቂ ከሆኑ ድምፃውያን አንዷ አድርጓታል።

​ ከሙዚቃ ባሻገር፦ ኪድጆ ከመድረክ ባለፈ ባቋቋመችው 'ባቶንጋ' ፋውንዴሽን አማካኝነት በመላው አፍሪካ የሚገኙ ሴቶች እና ወጣቶችን ታበቃለች። በተጨማሪም ለአዲሱ ትውልድ የአፍሪካ ከዋክብት መነሳሳትን በመፍጠር፤ በባሕል የበለፀጉ የአኀጉሪቱ የሙዚቃ ሀብቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ጎልተው እንዲወጡ በማድረግ ላይ ትገኛለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0