የሶማሊያ አየር መንገድ ከ35 ዓመታት በኋላ በመስከረም ወር ዳግም በረራ ሊጀምር ነው
የሶማሊያ አየር መንገድ ከ35 ዓመታት በኋላ በመስከረም ወር ዳግም በረራ ሊጀምር ነው
የሶማሊያ ሲቪል ኤቪዬሽን ባለሥልጣን የሀገሪቱ ብሔራዊ አየር መንገድ ወደ አገልግሎት እንደሚመለስ አረጋግጧል። ይህም እ.ኤ.አ በ1991 ከተቀሰቀሰው የእርስ በርስ ጦርነት ጀምሮ የሚሠራ የአየር መንገድ ላልነበራት ሀገር ትልቅ ስኬት ተደርጎ ተወስዷል።
ዋና ዋና ነጥቦች፦
የአውሮፕላን ስብስብ፦ አየር መንገዱ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 በተደረገ ስምምነት ባገኛቸው ሁለት ኤርባስ ኤ320 አውሮፕላኖች ሥራውን የሚጀምር ሲሆን የበረራ አውታሩ እያደገ ሲሄድ ተጨማሪ አውሮፕላኖች ይካተታሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የበረራ መስመር፦ በምሥራቅ አፍሪካ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ እና በአውሮፓ የሚገኙ ታሪካዊ የበረራ መዳረሻዎችን ጨምሮ የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ የበረራ መስመሮችን ለማካተት አቅዷል።
ዝግጅት፦ ወደ ሥራ ለመመለስ የሚደረገው ዝግጅት በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የሚገኝ ቢሆንም፤ አየር መንገዱ አሁንም የቁጥጥር ፈቃዶችን ማግኘት እንዲሁም የሠራተኞች፣ የጥገና እና የሥራ ማስኬጃ ሥርዓቶች መሟላታቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል።
በረራው ሶማሊያ የአቪዬሽን ዘርፏን ለመገንባት፣ ትስስር ለመፍጠር እና ከውጭ አየር መንገዶች ጥገኝነት ለመላቀቅ የምታደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው። ከዚህ ቀደም አየር መንገዱን ለመመለስ የተደርጉ በርካታ ሙከራዎች ሲዘገዩ ቆይተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X