ቤት የሚያህል የስፔስ ኤክስ ሮኬት ስብርባሪ ጨረቃ ላይ ተከስክሶ 18 ሜትር ስፋት ያለው ጉድጓድ ፈጠረ

ሰብስክራይብ

ቤት የሚያህል የስፔስ ኤክስ ሮኬት ስብርባሪ ጨረቃ ላይ ተከስክሶ 18 ሜትር ስፋት ያለው ጉድጓድ ፈጠረ

የስፔስ ኤክስ ፋልኮን 9 ሮኬት ሁለተኛ እርከን ስብርባሪ በሰዓት 9,000 ኪሎ ሜትር ፍጥነት ጨረቃ ላይ ከተከሰከሰ በኋላ የተፈጠረውን 18 ሜትር ስፋት ያለው ጉድጓድ (ክሬተር) የሚያሳዩ ምስሎችን ናሳ ይፋ አድርጓል። ሮኬቱ የብሉ ጎስት እና የጃፓኑን ሪዚሊየንስ የጨረቃ መንኮራኩሮችን አሳፍሮ እ.አ.አ በጥር 2025 ነበር የመጠቀው።

መንኮራኩሮቹን በተፈለገው ምህዋር ላይ ካደረሰ በኋላ፤ የሮኬቱ ሁለተኛ እርከን ወደ መሬት ተመልሶ በከባቢ አየር ውስጥ ለመቃጠል የሚያስችል በቂ ነዳጅ በማጣቱ ጨረቃ ላይ ሊከሰከስ ችሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0