የዓለም እና የአውሮፓ ሻምፒዮን ፓትሪክ ቪዬራ የሴኔጋል ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ዋና አሠልጣኝ ሆኖ ተሾመ
12:15 19.08.2026 (የተሻሻለ: 12:24 19.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዓለም እና የአውሮፓ ሻምፒዮን ፓትሪክ ቪዬራ የሴኔጋል ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ዋና አሠልጣኝ ሆኖ ተሾመ
ትውልደ ሴኔጋላዊው የ50 ዓመቱ አሠልጣኝ፤ ባለፈው ወር ከኃላፊነቱ የለቀቀው ፓፕ ቲያውን እንደሚተካ የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
ቁልፍ መረጃዎች፦
የአሠልጣኝነት ታሪክ፦ ቪዬራ በቅርቡ ያሠለጠነው የጣሊያኑን ክለብ ጄኖዋ (2024–2025) ነበር። በተጨማሪም ኒው ዮርክ ሲቲ፣ ኒስ፣ ስትራስቦርግ እና ክሪስታል ፓላስን አሠልጥኗል።
የተጫዋችነት ታሪክ፦ የቀድሞው የመሃል ሜዳ ተጫዋች ለአርሰናል፣ ኤሲ ሚላን፣ ጁቬንቱስ፣ ኢንተር ሚላን እና ማንችስተር ሲቲ ተጫወቶ፤ አምስት የጣሊያን ሊግ ዋንጫዎችን፣ ሦስት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን እና አምስት የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎችን አንስቷል።
ዓለም አቀፍ ስኬት፦ ቪዬራ በ1998 የዓለም ዋንጫ እና በ2000 የአውሮፓ ሻምፒዮና ባሸነፈው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ቁልፍ ተጫዋች ነበር።
የቀድሞው አሠልጣኝ፦ ፓፕ ቲያው ሴኔጋል በዓለም ዋንጫው የ32ኛ ዙር ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ከቤልጂየም ጋር ተጋጥማ በጭማሪ ሰዓት (2–3) በመሸነፍ ከውድድሩ መሰናበቷን ተከትሎ ሐምሌ 5 ኃላፊነቱን ለቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X