ባለሀብቶች ለዳንጎቴ የ2 ቢሊዮን ዶላር የአክሲዮን ገበያ ጅማሮ 400 ሚሊዮን ዶላር ቃል ገቡ
11:09 19.08.2026 (የተሻሻለ: 11:14 19.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ባለሀብቶች ለዳንጎቴ የ2 ቢሊዮን ዶላር የአክሲዮን ገበያ ጅማሮ 400 ሚሊዮን ዶላር ቃል ገቡ
ትልቁን የአፍሪካ የድፍድፍ ነዳጅ ማጣሪያ የማምረት አቅም በቀን ከ700 ሺህ ወደ 1.4 ሚሊዮን በርሜል ለማሳደግ፤ ዳንጎቴ በመስከረም ወር ወይም አጋማሽ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚያካሂደው ይፋዊ የአክሲዮን ሽያጭ እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር ለመሰብሰብ አቅዷል። ባለሀብቶች ከወዲሁ ከታለመው ገንዘብ ውስጥ 400 ሚሊዮን ዶላር ቃል እንደገቡ አንድ የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
◀ የቀደመው ዙር፦ ይህም ከተጠበቀው በላይ ከፍተኛ ተፈላጊነት ካገኘው የ2.5 ቢሊዮን ዶላር የግል የአክሲዮን ሽያጭ ቀጥሎ የመጣ ሲሆን አክሲዮኖቹ ለአፍሪካ እና ካሪቢያን የሉዓላዊ ሀብት ፈንዶች እና ተቋማዊ ባለሀብቶች እየቀረቡ መሆኑ ተገልጿል።
ስትራቴጂካዊ አስፈላጊነት፦ ማጣሪያው የናይጄሪያን የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት፣ የወጪ ንግድን ለማሳደግ እና በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ሳቢያ የተከሰተውን የቀጣናውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ከፍተኛ ሚና አለው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X