ኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ጋቦን የሰላም፣ ደህንነት እና ኢኮኖሚ ትብብራቸውን አጠናከሩ
17:58 16.08.2026 (የተሻሻለ: 18:04 16.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ጋቦን የሰላም፣ ደህንነት እና ኢኮኖሚ ትብብራቸውን አጠናከሩ
ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሴከዲ በጋቦን ባደርጉት ጉብኝት ሦስት የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸውን ከሁለቱ ሀገራት ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤቶች የወጡ መግለጫዎች አመልክተዋል።
የተፈረሙት ሰነዶች የሚከተሉትን ያጠቃልላሉ፡-
መደበኛ የፖለቲካ እና የዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ማቋቋም፣
የእርስ በእርስ የቪዛ ነፃ መብት ስምምነት፣
የንግድ ግንኙነቶችን ማጠናከርን ጨምሮ አጠቃላይ የትብብር ስምምነት።
ለአፍሪካ ኢንዱስትሪያላይዜሽን፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እና ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ የሆኑት የአኀጉሪቱ ተፈጥሮ ሀብቶች የሀገር ውስጥ እሴት ልዩ ትኩረት እንደተሰጠውም በመግለጫው ተጠቁሟል።
"አፍሪካ አሁን የተፈጥሮ ሀብቷን በገዛ ምድሯ እሴት ጨምራ ማዘጋጀት በመቻሏ ደስተኞች ነን" ሲሉ የጋቦን ፕሬዚዳንት ብሪስ ኦሊጊ ኑጌማ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X