ሀገር አቀፍ ማስፋፊያዎችን ተከትሎ የኢትዮጵያ የግብርና ሜካናይዜሽን 7 ሚሊዮን ሄክታር ደረሰ

ሰብስክራይብ

ሀገር አቀፍ ማስፋፊያዎችን ተከትሎ የኢትዮጵያ የግብርና ሜካናይዜሽን 7 ሚሊዮን ሄክታር ደረሰ

ኢትዮጵያ ዘንድሮ በዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎች የታረሰውን መሬት መጠን ወደ 7 ሚሊዮን ሄክታር በማሳደግ፤ የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ ለማዘመን እና የምግብ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ትልቅ እመርታ አስመዝግባለች።

በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ተሾመ ገለቱ፤ “ይህ ስኬት የተመዘገበው የግብርና ሜካናይዜሽንን በመላው ሀገሪቱ በማስፋት ነው” ሲሉ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልጸዋል።

አበይት የግብርና አሃዞች በአጭሩ፦

7 ሚሊዮን ሄክታር፡ ዘንድሮ በዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎች የታረሰ አጠቃላይ የግብርና መሬት።

9.75 ሚሊዮን ሄክታር፡ ከታቀደው 16 ሚሊዮን ሄክታር ውስጥ በአሁኑ ወቅት ስንዴ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ገብስ እና ሩዝን ጨምሮ በዋና ዋና ሰብሎች የለማ።

4.36 ሚሊዮን ሄክታር / 115 ሚሊዮን ኩንታል፡ በበልግ ወቅት የተሸፈነ የመሬት መጠን እና የታቀደ የምርት መጠን።

22.36 ሚሊዮን ሄክታር፡ ባለፈው ዓመት ከለማው 20.4 ሚሊዮን ሄክታር በመነሳት፤ ለመጪው የመኸር ወቅት የታቀደ ከፍተኛ የልማት ግብ።

 

ግብርና ሚኒስቴር በአሁኑ ወቅት ለኩታ ገጠም እርሻ ሞዴሎች ቅድሚያ እየሰጠ እንደሚገኝ እና ለግብርና ምርቶች ቀጥተኛ የገበያ ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እየሠራ እንደሆነ ገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0