የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋዜጠኛ በፈረንሳይ አምባሳደር ቅሌት ዙሪያ 'የተደራጀ የዝሙት መረብ' መኖሩን ገለጹ
15:13 16.08.2026 (የተሻሻለ: 15:14 16.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋዜጠኛ በፈረንሳይ አምባሳደር ቅሌት ዙሪያ 'የተደራጀ የዝሙት መረብ' መኖሩን ገለጹ
ጉዳዩ "ከአግባብ ውጪ የሆነ ባህሪ" ያለፈ እና "በደንብ የተደራጁ የዝሙት ደላሎች መረብን" ያሳተፈ እንደሚመስል በማዕከላዊ አፍሪካ "ኤክሊፕስ ዲአፍሪክ" የተሰኘው የመገናኛ ብዙኃን ዋና አዘጋጅ ፕሪንስቪያኔ ቡአንጋ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የፈረንሳይ አምባሳደር ብሩኖ ፉሼ ወጣት ሴቶችን ወደ መኖሪያ ቤታቸው አስገብተዋል በሚል በተሰነዘረባቸው ክስ የሥነ-ምግባር ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ቀደም ሲል መገናኛ ብዙኃን ዘግበው ነበር።
"ይህ ወጣት የማዕከላዊ አፍሪካ ሴቶችን የዋህነት እና ተጋላጭነት በመጠቀም ጥቃት የሚያደርሱ የወንጀለኞች እና የጾታ አዳኞች ሰፊ መረብ ነው" ብለዋል ቡአንጋ።
አክለውም፤ ከአምባሳደሩ ጋር ግንኙነት ከነበራቸው ሴቶች መካከል አንዳንዶቹ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች እንደሆኑ ለሴቶቹ ቅርብ የሆኑ ሰዎች መናገራቸውን ገልጸዋል።
ወጣት ሴቶቹን ዝም ለማስባል አንዳንዶቹ ግንኙነቶች በቪዲዮ ይቀረፁ እንደነበርም አስረድተዋል።
ቡአንጋ፤ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ባለሥልጣናት በጉዳዩ ዙሪያ ምርመራ እንዲጀምሩ እና ማብራሪያ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X