ኢትዮጵያ፣ ኬንያና ደቡብ ሱዳን የላፕሴት ፕሮጀክት የፋይናንስ ቁርጠኝነታቸውን ሊከልሱ ነው

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ፣ ኬንያና ደቡብ ሱዳን የላፕሴት ፕሮጀክት የፋይናንስ ቁርጠኝነታቸውን ሊከልሱ ነው

 

ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ለ25 ቢሊዮን ዶላሩ የላሙ ወደብ-ደቡብ ሱዳን-ኢትዮጵያ ትራንስፖርት ኮሪደር ልማት የሚያደርጉትን የፋይናንስ አስተዋጽኦ በድጋሚ ለመገምገም ዝግጅት እያደረጉ ነው።

 

ይህ ግዙፍ ቀጣናዊ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክት ሦስቱን ሀገራት በጥልቅ የባሕር ወደቦች፣ በነዳጅ መስመሮች፣ በየብስ መንገድ እና በባቡር መስመር ለማገናኘት የተነደፈ ነው።

 

የላፕሴት መስመር ዓላማዎች፦

 

🟠 የተሻሻለ ትስስር እና ሎጂስቲክስ፦ ወደብ አልባ ለሆኑ ሀገራት አስተማማኝ የባህር በር መዳረሻን ይሰጣል፣ የቀጣናውን የባቡር አሠራር ደረጃውን የጠበቀ ያደርጋል እንዲሁም በዋና ዋና መንገዶች ላይ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ በማቃለል አጠቃላይ የትራንስፖርት ወጪን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል።

 

🟠 የኢኮኖሚ እና የኢንዱስትሪ እድገት፦ የጅምላ ሸቀጦችን በብቃት ማንቀሳቀስ ማስቻል፣ የገበያ ተደራሽነትን ማሻሻል እንዲሁም በግንባታ እና በሥራ ሂደት ውስጥ ሰፊ የሥራ እድሎችን በመፍጠር የቀጣናውን ትስስር፣ የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና የሀብት ልማት ያበረታታል። -

 

🟠 የአካባቢን ዘላቂነት ማረጋገጥ፦ በኤሌክትሪክ ባቡር ትራንስፖርት አማካኝነት የካርቦን ልቀትን በመቀነስ እና ትይዩ በሆኑ የመንገድ ኔትወርኮች ላይ ያለውን የጥገና ጫና በማቃለል ለከባቢ አየር ተስማሚ የሆነ የትራንስፖርት ስርዓትን ያበረታታል።

ከሦስቱ አጋር ሀገራት የተውጣጡ የመንግት የሥራ ኃላፊዎች ቅድሚያ የሚሰጧቸው ሀገራዊ ጉዳዮችን ለማጣጣም እና ለፕሮጀክቱ ትግበራ የተሻሻለ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት በቀጣይ በሚካሄዱ ቀጣናዊ ስብሰባዎች ላይ ይመክራሉ።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0