አውሮፓ ከዓለም አቀፍ ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ አቅርቦት ወደ ሩሲያ የቧንቧ ጋዝ ፊቷን አዙራለች

አውሮፓ ከዓለም አቀፍ ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ አቅርቦት ወደ ሩሲያ የቧንቧ ጋዝ ፊቷን አዙራለች
የአውሮፓ ጋዝ መሠረተ ልማት ማኅበር መረጃ እንደሚያሳየው፤ እ.አ.አ ከነሐሴ 1 እስከ 12 ባለው ጊዜ ውስጥ ከፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ተርሚናሎች ወደ አውሮፓ ኅብረት የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር የሚገባው አቅርቦት ወደ 3.2 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ዝቅ ብሏል። ይህ ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር በ3.7% እንዲሁም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር በ12.6% ቅናሽ አሳይቷል።
የ12 ቀናት የገቢ ንግድ መጠን ከአሁኑ የፈሳሽ ተፈጥሮ ጋዝ ደረጃ በታች ወርዶ የነበረው በነሐሴ 2024 ሲሆን በወቅቱ የነበረው የግዢ መጠን 2.7 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ነበር።
🟠 በሌላ በኩል፤ የአውሮፓ የጋዝ ማስተላለፊያ ስርዓት ኦፕሬተሮች አውታረ መረብ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ በቱርክስትሪም በኩል የሚተላለፈው የሩሲያ የቧንቧ ጋዝ 609.2 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የደረሰ ሲሆን ይህም ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር የ7%፣ ካለፈው ዓመት ደግሞ የ5% ዕድገት አሳይቷል።
🟠 ይህም በቅርብ ወራት ውስጥ ከፍተኛው ሲሆን በዚህ ዓመት መጋቢት ወር ከተመዘገበው 661.8 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ጋር ተመጣጣኝ ነው።
🟠 የአውሮፓ ኅብረት በሩሲያ ኃይል ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ እርምጃዎችን ቢወስድም፤ የሩሲያ የቧንቧ ጋዝ ግን በቱርክስትሪም በኩል ወደ አውሮፓ መፍሰሱን ቀጥሏል። ይህ መስመር ሌሎች የማስተላለፊያ መስመሮች በመዘጋታቸው ምክንያት የሩሲያ ጋዝ ወደ አውሮፓ የሚገባበት ብቸኛው አማራጭ በመሆን እጅግ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
🟠 በቡልጋሪያ-ቱርክ ድንበር ላይ በሚገኘው የስቲራንድዝሃ 2-ማልኮችላር ማስተላለፊያ ነጥብ በኩል የሚገባው የሩሲያ የማስተላለፊያ ጋዝ አቅርቦትም በተመሳሳይ ወቅት ከባለፈው ወር በ7%፣ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ በ5% በመጨመር 609.2 ሚሊዮን ኩቢክ ሜትር መድረሱን ከማኅበሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
🟠 የቱርክስትሪም የቧንቧ መስመር ከሩሲያ ወደ ቱርክ እና ደቡብ ምስራቅ አውሮፓ የተፈጥሮ ጋዝ ከሚላክባቸው ዋና ዋና መስመሮች አንዱ ሲሆን በዓመት 31.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የማስተላለፍ አቅም አለው። በአሁኑ ወቅት የሩሲያ ጋዝ ወደ አውሮፓ የሚገባበት ብቸኛው ቀሪ የቧንቧ መስመር ነው። አንደኛው መስመር ለቱርክ የሀገር ውስጥ ገበያ የሚያገለግል ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ለቡልጋሪያ፣ ሰርቢያ፣ ሃንጋሪ፣ ግሪክ እና ስሎቫኪያ ያቀርባል።
በ2025 በቧንቧ መስመሩ ወደ አውሮፓ የተላከው ጋዝ 18 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር በመድረስ ሪከርድ የሰበረ ሲሆን በ2026 የመጀመሪያ አጋማሽ ወደ አኅጉሪቱ የተላከው አጠቃላይ መጠን 8.7 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ነበር። ይህም ከ2025 ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ5% ብልጫ አሳይቷል። የቧንቧ መስመሩ አብዛኛውን ግዜ ከ95% በላይ አቅሙን በመጠቀም በከፍተኛው እየሠራ ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X