ቻይና ወደ አውሮፓ የሚደረግ የመርከብ ጉዞን በግማሽ የሚቀንስ አዲስ የአርክቲክ አቋራጭ መንገድ ከፈተች
ቻይና ወደ አውሮፓ የሚደረግ የመርከብ ጉዞን በግማሽ የሚቀንስ አዲስ የአርክቲክ አቋራጭ መንገድ ከፈተች
የቻይናው የኮንቴነር መርከብ ድርጅት፣ "ሲ ሌጀንድ ሺፒንግ" ንብረት የሆነችው "ዱባይ ታወር" የኮንቴነር መርከብ ከኒንግቦ-ዙሻን ወደብ ተነስታለች፤ ይህም በሰሜን ምሥራቅ መስመር በኩል የሚደረገውን የቻይና-አውሮፓ የአርክቲክ ኤክስፕረስ ሳምንታዊ መደበኛ የበጋ ጉዞ አስምራለች።
🟠 ባለአንድ አቅጣጫው ጉዞ በስዊዝ ካናል በኩል ይወስድ የነበረውን 40 ቀናት ገደማ የሚፈጅ ጉዞ ወደ 20 ቀናት ዝቅ በማድረግ፣ ከጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች እና ከተጨማሪ ወጪዎች ስጋት ያድናል።
🟠 መርከቧ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው እና ለሙቀት ተፅዕኖ ተጋላጭ የሆኑ አዳዲስ የኃይል ምርቶችን (የኃይል ባትሪዎችን፣ የፀሐይ ብርሃን ሞጁሎችን እና የኃይል ማከማቻ ሥርዓቶችን) ጭናለች፡፡
🟠 የበረዶ መቋቋም አቅም ባላቸው መርከቦች (አንዳንዶቹ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ) በዚህ ዓመት ቢያንስ ስምንት ጉዞዎች ታቅደዋል፡፡
🟠 የጉዞው ወቅታዊ መርሃ-ግብር ከሃምሌ እስከ ጥቅምት የሚዘልቅ ሲሆን፣ የመካከለኛ ጊዜ ግቡ ደግሞ የመርከብ ጉዞ ጊዜውን ደረጃ በደረጃ በማራዘም በየዓመቱ የነበረውን ወደ አራት ወራት መደበኛ አገልግሎት ማሳደግ ነው።
ቻይና የዋልታ የሐር መንገድን መደበኛ የንግድ መስመር በማድረግ የ"ቀበቶ እና መንገድ" ትብብርን የምታጠናክር ሲሆን፣ ለዓለም አቀፍ ንግድም አዲስ ጽናትን እያበረከተች ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X