የአፍሪካ ሀገራት “ለስደት የሚዳርጉ ሁኔታዎችን ለመቅረፍ” በጥምረት መሥራት አለባቸው – የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት

ሰብስክራይብ

የአፍሪካ ሀገራት “ለስደት የሚዳርጉ ሁኔታዎችን ለመቅረፍ” በጥምረት መሥራት አለባቸው – የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት

"ሕዝቦቻችን የስደት ውጤት ናቸው። [...] ግጭትን፣ አለመረጋጋትን፣ የአስተዳደር ድክመት፣ ድህነትን እና ማኅበራዊ አለመግባባትን እልባት ለመስጠት በጋራ መሥራት አለብን” ሲሉ ሲሪል ራማፎሳ በ46ኛው የደቡብ አፍሪካ ልማት ማኅበረሰብ ጉባኤን አስመልክቶ በክዋዙሉ-ናታል ዩኒቨርሲቲ ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል።

ራማፎሳ እንዳሉት ከሆነ፣ ቀጣናዊ ውህደት በመጨረሻም ሰዎች ከተቀመጡ መርሆዎች እና ሕግጋት ጋር በተጣጣመ መልኩ በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ ማስቻል አለበት፤ ይህም ስደት በምርጫ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባዋል፡፡

“እኩል ኢኮኖሚያዊ እድሎችን መፍጠር እና አካታች የአስተዳደር ተቋማትን መገንባት አለብን” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

46ኛው የደቡብ አፍሪካ ልማት ማኅበረሰብ ጉባኤ ነሐሴ 11 ቀን በደርባን ከተማ ለማካሄድ መርሃግብር ተይዟል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0