ኢትዮጵያ እና ዮርዳኖስ የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
14:45 15.08.2026 (የተሻሻለ: 14:54 15.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ዮርዳኖስ የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተል፣ የጋራ እንቅስቃሴዎችን የሚያስተባብር እና ለወደፊት ኢኮኖሚያዊ ትብብር ስትራቴጂካዊ መመሪያ የሚሰጥ “የዮርዳኖስ-ኢትዮጵያ የጋራ የንግድ ምክር ቤት” ይቋቋማል።
የስምምነቱ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች፦
መረጃና አቅም ግንባታ፦ የገበያና ኢንቨስትመንት መረጃዎችን መለዋወጥ፣ የሥልጠናና አቅም ግንባታ ሥራዎችን በጋራ መስራት።
ኢንተርፕራይዞችና ፈጠራ፦ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን፣ አዳዲስ ሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም አረንጓዴ ኢኮኖሚን መደገፍ።
ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፦ በኢ-ኮሜርስ፣ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ታዳሽ ኃይል ላይ ትኩረት ማድረግ።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሰብሳቢ አባፊራ አባጆቢር እና የዮርዳኖስ የንግድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ኻሊል አል-ሃጅ ተውፊቅ ፈረመውታል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X