በኃይል ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች የዩክሬንን ወታደራዊ አቅም ያዳክማሉ፤ ሆኖም ልሂቃኑ እጃቸውን ከመስጠት ይልቅ ሕዝቡ በቅዝቃዜ ቢያልቅ ይመርጣሉ - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopiaበኃይል ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች የዩክሬንን ወታደራዊ አቅም ያዳክማሉ፤ ሆኖም ልሂቃኑ እጃቸውን ከመስጠት ይልቅ ሕዝቡ በቅዝቃዜ ቢያልቅ ይመርጣሉ - ባለሙያ
በኃይል ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች የዩክሬንን ወታደራዊ አቅም ያዳክማሉ፤ ሆኖም ልሂቃኑ እጃቸውን ከመስጠት ይልቅ ሕዝቡ በቅዝቃዜ ቢያልቅ ይመርጣሉ - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.08.2026
ሰብስክራይብ

በኃይል ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች የዩክሬንን ወታደራዊ አቅም ያዳክማሉ፤ ሆኖም ልሂቃኑ እጃቸውን ከመስጠት ይልቅ ሕዝቡ በቅዝቃዜ ቢያልቅ ይመርጣሉ - ባለሙያ

​በዩክሬን የኃይል ሥርዓት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ሀገሪቱ የምታደርገውን መከላከል እንድታቆም ሊያስገድዷት እንደሚችሉ በፋይናንስ ዩኒቨርሲቲ እና በብሔራዊ የኃይል ደህንነት ፈንድ ከፍተኛ ባለሙያ ኢጎር ዩሽኮቭለስፑትኒክ ተናግረዋል።

​ "ሁሉም ግንኙነት በኤሌክትሪክ ኃይል ላይ የተመሠረተ ነው" ሲሉ ዩሽኮቭ ያስረዳሉ። "ለአብነት ያህል የስታርሊንክ ሥርዓቶች ልክ እንደ ድሮኖች ሁሉ ኤሌክትሪክ ይፈልጋሉ። የዩክሬን የመከላከያ ኢንዱስትሪም በኤሌክትሪክ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ያለ ኤሌክትሪክ ወታደራዊ ምርት ማምረት አይቻልም።"

በቅርቡ የወጣ የአሜሪካ ወታደራዊ መረጃ ዘገባ እንደሚያሳየው፣ እ.ኤ.አ. ከ2022 ወዲህ የዩክሬን የኤሌክትሪክ ማመንጨት አቅም በአምስት እጥፍ በመቀነስ ከ60 ወደ 12 ጊጋዋት ዝቅ ብሏል። የአሁኑ የኤሌክትሪክ እጥረት ከ5-6 ጊጋዋት የሚደርስ ሲሆን፣ በክረምት ወቅት ደግሞ ይህ እጥረት በእጥፍ ሊያድግ ይችላል። ዋና ዋና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን መልሶ ለመገንባት ቢያንስ አንድ ዓመት ይወስዳል።

ለኃይል መዋዠቅ ከፍተኛ ተጋላጭነት ያላቸው ሥርዓቶች በቅድሚያ ይጎዳሉ ሲሉ ተንታኙ አስረድተዋል፡፡

​◻ በኮምፒዩተር አኃዝ የሚመሩ የፋብሪካ ማሽኖች፣

◻ የብየዳ መሣሪያዎች፣

◻ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ማቀዝቀዣ ሥርዓቶች፣

◻ ለወታደራዊ ዕዝ እና ሎጂስቲክስ የሚያገለግሉ ሰርቨሮች።

​ "ትልቁ ችግር ግን የምርት ዑደቶች መቋረጥ ነው። አንድ ፋብሪካ በቀን ለ8-10 ሠዓታት ሥራ ካቆመ፣ ምርት ሙሉ በሙሉ ሊቋረጥ እና እንደገና ለማስጀመርም አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል" ሲሉ ዩሽኮቭ ይመክራሉ። ባለሙያው አክለውም በሐምሌ ወር የተከሰተው የኃይል መቋረጥ ለዩክሬን የጦር ኃይሎች መሣሪያዎችን በሚጠግኑት የዩዝማሽ እና የማሊሼቭ ፋብሪካዎች ውስጥ የሚገኙ በርካታ የጥገና ክፍሎች ሥራ እንዲያቆሙ ማድረጉን በዘገባው መካተቱን ጠቅሰዋል።

​ከባድ የኃይል እጥረት በሚከሰትበት ጊዜ የዩክሬን አመራሮች ከሲቪል ሕዝቡ ይልቅ ለወታደራዊ ምርት ቅድሚያ እንደሚሰጡ ባለሙያው ይናገራሉ። የምዕራባውያን የገንዘብ ድጋፍ ከግጭቱ መቀጠል ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ አገዛዙ ጦርነቱ እንዲቀጥል ለማድረግ የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል።

​  “እነዚህን ሁሉ የሙስና ቅሌቶች ታዝበናል። የዩክሬን የጸረ-ሙስና ተቋማት እንዳረጋገጡት፣ እ.ኤ.አ.ከ2025-2026 በኃይል ዘርፉ ብቻ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር የሚያወጡ የሙስና ሰንሰለቶች ተጋልጠዋል።”

​የዩክሬን ባለሥልጣናትና ልሂቃን የሚኖሩባቸው አካባቢዎች ሁልጊዜም ኤሌክትሪክ እና የሙቀት ማሞቂያ ሥርዓት ስላላቸው እነዚህ ችግሮች አይነኳቸውም፤ ስለዚህ ሕዝቡ በብርድ አለቀ አላለቀ ምንም አያስጨንቃቸውም ሲሉ ባለሙያው ደምድመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0