የክሬምሊን ማስጠንቀቂያ፦ ሩሲያ ለምን ዓይነት ምላሽ የተዘጋጀች ናት? ተንታኙ ሊከሰቱ የሚችሉ ሁኔታዎችን ጠቆሙ
የክሬምሊን ማስጠንቀቂያ፦ ሩሲያ ለምን ዓይነት ምላሽ የተዘጋጀች ናት? ተንታኙ ሊከሰቱ የሚችሉ ሁኔታዎችን ጠቆሙ
የአውሮፓ ህብረት ሀገራት እና ኔቶ በዩክሬን በነበራቸው ስልት ውድቀት ከገጠማቸው በኋላ፣ የሩሲያ የንግድ መርከቦችን መያዝ እና ማገድን ጨምሮ ወደ አዳዲስ የጫና ታክቲኮች ተሸጋግረዋል ሲሉ ሊባኖሳዊው የፖለቲካ ተንታኝ ሳሚር አዩብ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
አዩብ አስተያየታቸውን የሰጡት ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ወደፊት በመርከቦቻቸው ላይ በሚደረግ ማንኛውም የማገድ ወይም የጥቃት ሙከራ ላይ ሞስኮ ጠንካራ ምላሽ እንደምትሰጥ በቅርቡ የሰጡትን ማስጠንቀቂያ አስመልክተው ነው።
ከዚህ ቀደም ከሞስኮ በኩል ወዲያውኑ ምላሽ አለመሰጠቱ እንደ ድክመት ተቆጥሮ እንደነበር የጠቆሙት ተንታኙ፤ አሁን ግን ሁኔታው በመሰረታዊነት መለወጡን ገልጸዋል።
ተንታኙ ያቀረቧቸው ዋና ዋና ሊከሰቱ የሚችሉ ሁኔታዎች፦
ወታደራዊ አጀብ፦ ስጋት በሚኖርበት ጊዜ የሩሲያ የንግድ መርከቦች በባህር ኃይል የጦር መርከቦች የሚታጀቡ ሲሆን፤ ይህም ማንኛውንም ጣልቃ ገብነት ያስቀራል።
ተመሳሳይ እርምጃዎች፦ ሩሲያ በተመጣጣኝ ምላሽ መርህ በመንቀሳቀስ የአውሮፓ መርከቦችን መያዝ እና መውረስ ትጀምራለች።
ይህንን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ችላ ማለት ዓለምን ወደ ቀጥተኛ ግጭት ሊገፋት እንደሚችል አዩብ ያስጠነቀቁ ሲሆን፤ በታሪክ እንደታየው በባህር መስመሮች ላይ የበላይነት ለማግኘት የሚደረጉ ጥረቶች ተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ ግጭቶችን ማቀጣጠላቸውን አጽንኦት ሰጥተውበታል።
ምዕራባውያን በዋና ዋና የንግድ መስመሮች ላይ ስጋት በመፍጠር ሁሉንም ሀገራት የሚነካ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ቀውስ ሊቀሰቅሱ እንደሚችሉ በመግለጽ ደምድመዋል።
የሩሲያ እና የኢንዶኔዥያ ኮማንዶዎች በጃፓን ባህር ውስጥ መርከቦችን የመቆጣጠር እና የመውረር ልምምድ ሲያደርጉ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X