የደቡብ አፍሪካ እና የዚምባብዌ ፕሬዝዳንቶች በካሪባ ሀይቅ የጀልባ መስመጥ አደጋ የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ
19:35 13.08.2026 (የተሻሻለ: 19:44 13.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ እና የዚምባብዌ ፕሬዝዳንቶች በካሪባ ሀይቅ የጀልባ መስመጥ አደጋ የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ
ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት የወጣ መግለጫ እንደሚያመለክተው፤ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ የ44 ሰዎችን ሕይወት በቀጠፈው በካሪባ ሀይቅ የጀልባ መስመጥ አደጋ ምክንያት ለዚምባብዌ ያላቸውን የጠነከረ አጋርነት ገልጸዋል።
"ለተረፉት ፈጣን ምህረትን እንመኛለን፤ ለተጎዱ ቤተሰቦች እና ማህበረሰቦች ድጋፍ ለመስጠት እና እፎይታን ለማስገኘት ሳይታክቱ ለሚሰሩ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችም ክብር እንሰጣለን" ሲሉ ፕሬዝዳንቱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኢመርሰን ምናንጋግዋ በአደጋው ለተጎዱ ቤተሰቦች አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርጉ ለባለስልጣናት መመሪያ ሰጥተዋል።
"የሚመለከታቸው አካላት በቦታው በመገኘት ለተጎጂዎች እና ለተረፉት ሰዎች ሙሉ የሕክምና፣ የቀብር እና የስነ-ልቦና ድጋፍ እየሰጡ ይገኛሉ" ሲሉ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው አስፈረዋል።
119 ሰዎችን ይዛ የነበረችው ጀልባ ማክሰኞ ዕለት በዚምባብዌ እና ዛምቢያ ድንበር በሚገኘው ካሪባ ሀይቅ ላይ ነበር የሰመጠችው።
በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪዲዮ አደጋው ከመከሰቱ ጥቂት ቀደም ብሎ የነበረውን ሁኔታ እንደሚያሳይ ተነግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X