አፍሪካ ከፋይናንስ ገደቦች ጋር በምትጋፈጥበት በዚህ ወቅት የሩሲያው "ኤ7" የክፍያ ሥርዓት አማራጭ ሊሆን ይችላል?

© telegram sputnik_ethiopiaአፍሪካ ከፋይናንስ ገደቦች ጋር በምትጋፈጥበት በዚህ ወቅት የሩሲያው "ኤ7" የክፍያ ሥርዓት አማራጭ ሊሆን ይችላል?
አፍሪካ ከፋይናንስ ገደቦች ጋር በምትጋፈጥበት በዚህ ወቅት የሩሲያው ኤ7 የክፍያ ሥርዓት አማራጭ ሊሆን ይችላል? - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.08.2026
ሰብስክራይብ

አፍሪካ ከፋይናንስ ገደቦች ጋር በምትጋፈጥበት በዚህ ወቅት የሩሲያው "ኤ7" የክፍያ ሥርዓት አማራጭ ሊሆን ይችላል?

የሩሲያው ፒኤስቢ ባንክ ፕሬዝዳንት ፒዮትር ፍራድኮቭ ከሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ የ"ኤ7" ዓለም አቀፍ የክፍያ ስርዓት አሰራርን እና በተለይም በአፍሪካ በሚገኙ ሦስተኛ ሀገራት ዘንድ እያደገ የመጣውን ፍላጎት አብራርተዋል።

እንደ እሳቸው ገለፃ ባንኩ ከበርካታ የአፍሪካ እና የእስያ ሀገራት ጋር በስፋት እየሰራ ይገኛል። በተለይም በግዙፏ የአኅጉሪቱ ኢኮኖሚ ናይጄሪያ የኤ7 ኩባንያ ይፋዊ ቢሮ ተከፍቷል። በአሁኑ ወቅት ወደ 250 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ያላት ናይጄሪያ በሚቀጥሉት ከ15 እስከ 20 ዓመታት ውስጥ ህዝቧ 400 ሚሊዮን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። በሰፊው ሲታይ ደግሞ የአፍሪካ አህጉር ህዝብ ቁጥር እስከ እ.ኤ.አ. 2050 ድረስ ወደ 2.5 ቢሊዮን ያድጋል ሲሉ አብራርተዋል።

"ይህ በገደቦች እና ማዕቀቦች ስርም ቢሆን የሚንቀሳቀስ እጅግ ግዙፍ ገበያ ነው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት አሁንም ቢሆን ማዕከላዊ ባንክ የላቸውም፤ ወደ አስር የሚጠጉ አሉ" ሲሉ ፒዮትር ፍራድኮቭ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህ አዲስ እንቅስቃሴ ከዓለም ኢኮኖሚ እጅግ ዝግ ከሆኑት ዘርፎች አንዱ በሆነው ድንበር ተሻጋሪ የክፍያ ስርዓት ላይ አማራጭ አሰራርን ለማቅረብ ከሚደረገው ጥረት የሚመደብ ነው።

እንደ ፍራድኮቭ ገለፃ፤ ኤ7 ከሩሲያ የንግድ ፍሰት ውጭ በሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ግብይቶች በሦስተኛ ሀገራት መካከል እርስ በእርስ ጥቅም ላይ መዋል ጀምሯል።

"ይህም ለሌሎች ሀገራት ራሱን የቻለ ገለልተኛ የክፍያ መሳሪያ በመሆኑ እጅግ ሳቢ እየሆነ መጥቷል" ሲሉ ተናግረዋል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0