የኢትዮጵያ ወጣቶች የሉዓላዊነታችን ፅኑ ማገር ናቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

የኢትዮጵያ ወጣቶች የሉዓላዊነታችን ፅኑ ማገር ናቸው
 የኢትዮጵያ ወጣቶች የሉዓላዊነታችን ፅኑ ማገር ናቸው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.08.2026
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ወጣቶች የሉዓላዊነታችን ፅኑ ማገር ናቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

በሀገሪቱ የህዝብ ስብጥር ውስጥ ወጣቱ ከፍተኛውን ቁጥር እንደሚይዝ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያን ከወጣቶቿ ነጥሎ ማየት አይቻልም ሲሉ ገልፀዋል።


"‎የኢትዮጵያ ወጣት መልካም ዓላማን አንግቦ የሚንቀሳቀስ፣ የለውጥ ዋነኛ ሞተርና የሉዓላዊነታችን ጽኑ ማገር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ወጣት የሀገሩን ታሪክ በአዲስ ብዕርና ብራና እየጻፈ ይገኛል። ሀገራችንን የኋሊት ጠፍንገው የያዟትን አጓጉል ልማዶች፣ አላስፈላጊ ንትርኮች፣ ጭቅጭቅ እና ግጭቶች በመራቅ የአሁን ወጣት በልማት ላይ አተኩሯል፣ ድህነትን ተጠይፏል።" ሲሉም በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።


'‎ሀገራዊ ርዕያችንን ዕውን ለማድረግ ሁላችንም በንቃት እየተጋን፣ በፍቅር እንድንመላለስ' ሲሉም የዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን አስመልከተው ጥሪ አቅርበዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0