ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ለሩሲያ ስፖርተኞች ተሳትፎ ይሁንታ ከሰጠ፤ አውሮፓ የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ ልታቋርጥ ትችላለች - የሩሲያ የውጭ የደህንነት አገልግሎት
14:34 11.08.2026 (የተሻሻለ: 14:44 11.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ለሩሲያ ስፖርተኞች ተሳትፎ ይሁንታ ከሰጠ፤ አውሮፓ የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ ልታቋርጥ ትችላለች - የሩሲያ የውጭ የደህንነት አገልግሎት
አገልግሎቱ በሰጠው መግለጫ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
▪ የአውሮፓ ልሂቃን የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሩሲያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እና በሩሲያውያን ስፖርተኞች ላይ ጥሎት የነበረውን ዕቀባ ለማንሳት ውሳኔ በማስተላለፉ ስጋት አድሮባቸዋል።
▪ የኦሊምፒክ ኮሚቴው ውሳኔ ምዕራባውያን ሩሲያን ከዓለም አቀፍ ስፖርት "ለማግለል" ሲያደርጉት የቆዩትን ጥረት ያከሽፋል በማለት አውሮፓ አቤት ብላለች።
▪ አውሮፓ ከፍተኛ ቁጥር ባላቸው የሩሲያ ስፖርተኞች እና የስፖርት ኃላፊዎች ላይ ተጨማሪ የቪዛ እገዳዎችን ለመጣል እያጤነች ነው።
የአውሮፓ ቢሮክራቶች 'በሩሲያ ጥላቻ' ታውረው የኦሊምፒክ እንቅስቃሴን ለማክሰም ተዘጋጅተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X